Friday, March 8, 2013

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም (ክፍል አንድ)

በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ 
የእቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ክብር፦

1. ፕሮቴስታንቶች እመቤታችን አያከብሯትም፣ ምልጃም አይጠይቋትም፣ በዓላቶቿንም አያከብሩም፤ አንዳንድ ቡድኖች ጭራሽ ጫጩት ከተፈለፈለ ወዲያ ዋጋ በሌለው እንቁላል ቅርፊት ሊመስሏት ይወዳሉ። ፕሮቴስታንቶች እመቤታችንን ላለማክበር የሚያደርጉት ይህ ሁሉ ተቃውሞ ምናልባት ካቶሊኮች ለእርሷ ከሚሰጧት የተጋነነና ቅጥ ያጣ ክብር የመጣ ይመስለኛል።

2. አንዳንድ ፕሮቴስታንት አንጃዎች ጭራሹን ደፋር ከመሆናቸው የተነሳ እመቤታችንን “እህታችን ማርያም” ብለው ይጠሯታል።

3. በተጨማሪም ፕሮቴስታንቶች ጌታችንን ከወለደች በኋላ የዮሴፍ ሚስት ሆና ኖራለች፣ ለዮሴፍ “የኢየሱስ ወንድሞች” ወይም “የጌታ ወንድሞች” በመባል የሚታወቁ ልጆችን ወልዳለታለች ይላሉ።

4. ፕሮቴስታንቶች እመቤታችን እንዳያከብሩ ደረጋቸው ሌላው ምክንያት ደግሞ በመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉማቸው “ጸጋን የተሞላሽ” የሚለውን የመላኩን ቃል “አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ” በሚለው ሐረግ በመለወጣቸው ነው ።

5. ፕሮቴስታንቶች እመቤታችን በ1980 ዓ/ም አዲሱ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉማቸው “አንቺ ጸጋን የተሞላብሽ ሰላም ላንቺ ይሁን እግዚአበሔር ከአንቺ ጋር ነው” ካለ በኋላ በቅንፍ ውስጥ “(አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ)” ብለው ፅፈዋል።