Monday, February 16, 2015

ስለ መካ ከተማ መያዝ (መሸነፍ)፦


(ከአስራ  ስምንት ዓመት በታች ማንበብ አይፈቀድም!)

            ሙሐመድም . . . ከዚህም ሌላ መካን በጦር ኃይል ለመያዝ ያደረገው ሃሳብ የተቀደሰ ስፍራ ነው፤ ስለ ሃይማኖት ግዴታ መካን መያዝ አለብን ብሎ ለተከታዮቹ አስረዳ። «መካውያን መካ ገብተን እንሰግድ ዘንድ ያልፈቀዱልን እንደኾነ ምን ማድረግ ይገባናል» ብለው ተከታዮቹ ቢጠይቁት፤ «እኔ የመጨረሻው ነቢይ፥ ሰይፌን ጨብጬ ተላክሁ፣ ሰይፉም፥ የመንግሥተ  ሠማያና የገሃነም መክፈቻ ነው። ስለ ሃይማኖት ሲሊ የሚመዝዙት ሰይፍ ዋጋ ያገኙበታል።» ሲል ሙሐመድ መለሰላቸው።

           . . . ሙሐመድ በዕድሜው እያረጀ ሄደ፣ እንደ ልቡ ለመራመድ አልደፈረም። የደም ሥሮቹም ደክመው ነበር። በአረብ ሃገር፥ ነቢይነቱንና መሪነቱ በመታወቁ መጠን፣ ዓለም በመላ የእስላም ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ግዛት ትኾን ዘንድ አለመ። መዲና ላይ የጦር ኃይሉን እንደ አደራጀና እንዳጎለመሰ ሁሉ በሌሎች ሃገሮችም የእስላምን ሃይማኖት የሚዘረጉትንና የሚያስፋፉትን የክብር መልክተኞችን ማደራጀት ጀመረ። እንዲህ ሲልም ለውጭ ሃገር መንግሥታት መሪዎች ጻፈ፤ ለሮም ቄሣር የጻፈው ደብዳቤ ከዚህ በታች የሚገኘው (የሚነበበው) ነው። ለሌሎችም ነገሥታት ሁሉ የጻፋቸው ደብዳቤዎች እንዲሁ ያሉ ነበሩ፦

Sunday, February 8, 2015

ንግሥት ሳባ፦

ንግሥት አዜብ፥ የንጉሥ ሠለሞንን ጥበብን ለማየትና ለመስማት እንደተገናኘችና ከሃገራችን የሚገኘውን አልማዝና ወርቅ እጅ መንሻ ሥጦታ እንዳበረከተችለት፤ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦ "ለንጉሡም መቶ ሃያ መክሊት ወርቅ፣ እጅግም ብዙ ሽቱ፣ የከበረም ዕንቍ ሰጠችው፤ የሳባ ንግሥት፥ ለንጉሡ ለሠሎሞን እንደ ሰጠችው ያለየሽቱ ብዛት ከዚያ ወዲያ አልመጣም ነበር።" (፩ኛ ነገ ፲፥፩-፲፫፤ ፪ኛ ዜና ፱፥፩-፲፪፤ ማቴ ፲፪፥፵፪፤ ሉቃ ፲፩፥፴፩)