Showing posts with label እንወቃቸው. Show all posts
Showing posts with label እንወቃቸው. Show all posts

Sunday, January 19, 2014

SARĀBĀMON OF NIKOU (ቅዱስ ሰራባሞን)


By Dr Amsalu Aefera Assistant Prof – SARĀBĀMON OF NIKOU IN ETHIOPIAN LITERATURE.

ስለ ቅዱስ ሰራባሞን ስንቶቻችን እናውቅ ይሆን? በዘመነ ሰማዕታት የተነሳ፣ አርዮስንና መሊጦስን በትምህርቱ የተቃወመና የረታ፣ ብዙ ገቢረ ተአምራትን የሠራ፣ የኒቅዩ (በግብጽ ውስጥ የምትገኝ ሀገረ ስብከት) ሊቀ ጳጳስና ሰማዕት ነው። እንመልከት። በረከቱ በሁላችንም ላይ ይደርብን።

St. Sarābāmon, Bishop of Nikou, lies among those important oriental saints whose reputation reached the Ethiopian Orthodox Church. According to his vita (see further below), he was a descendant of the proto-martyr Stephen and raised as a Jew in Jerusalem under the birth name of Simon.  After journeying to Alexandria, he was baptized by Archbishop Theonas (282-300), the 16th Pope of Alexandria, and then set about studying Scripture, including the Epistle of Ignatius and Balkiros.  He then became a monk in El-Zogag[1] monastery.  When the Alexandrian Patriarchate passed to Peter, the Seal of the Martyrs (300-311), Simon was made a patriarchal assistant, and later was appointed bishop of Nikou, with the ordained name of Sarābāmon, upon the death of John, the incumbent of that office.  The Ge‘ez version of the vita states:

Wednesday, December 11, 2013

አንደበተ ርቱዕ፥ አባ ፍስሐ



       ከደብረ ሊባኖስ ወደ አብተ ማርያም ገዳም ለመድረስ በእግር ጉዞ መሄድ ግድ ይላል። የመድረሻ ሰዓት፥ እንደ እግር ተገዦች (እንደሰዎች) ፍጥነት ይለያያል። እኛ ግን ወደ አንድ ሰዓት ከአርባ ደቂቃ አካባቢ ፈጅቶብን ደረስን።

በዛም፥ በአብተ ማርያም ገዳም አካባቢ ከሚኖሩ አበው ዘንድ ጎራ በማለት አባ ፍስሐ አገኘናቸው። እርሳቸው በመንፈሳዊ ሕይወታቸው የበቁ አባት ናቸው። አባ ፍስሐ፥ ምክራቸው፣ ተግሳፃቸው፣ ትምህርታቸው፤ እጅግ እጹብ ድንቅ ነው።

ከአንደበታቸው በሚወጣው ፍጹም መንፈሳዊ ምግብ፦ ነፍስህ ሐሴት ስታደርግ ታስተውላለህ፣ ሕይወት ትማረካለች፤ ተመስጧቸው፥ ህሊናን ወደ መንፈሳዊ ተመስጦ ውስጥ ይመራዋል፣ በመንፈሳዊ ተጋድሎዋቸው የሕይወታቸው ምርኮኛ እንድትሆን አንዳች የመንፈስ ቅዱስ ምሪት ያነሳሳሃል። እድሜያቸውን በሙሉ ለእግዚአብሔር አገልግሎት የገበሩ አባት ናቸው።


Saturday, May 25, 2013

የዶ/ር እጓለ ገብረ ዩሐንስ አጭር የሕይወት ታሪክ

ደራሲ / እጓለ ገብረ ዩሐንስ ከጻፉት መፅሐፍ ስለ ሞራል ድቀት ብፁዓን ንጹሐነ ልበ ስለ ክርስቲያን ምግባር መሠረት በሚል ለንባብ ካበቁት የተወሰደ። 

      ሀገር፣ መንደር፣ ቤት ንብረቱን ትቶ ወደ ሩቅ የሄደ ሰው ባይተዋር ይባላል። ይህ ስያሜ በኑሮ አድራሻ መለወጥ ብቻ ምክንያቱን የሚያገኝ አይደለም።   የመንፈስ ባይተዋርነትም አለ። ሰው ከነበረበት ቦታ ወደ ሌላ ሳይዘዋወርም ለአዲስ አስተሳሰብ፣ ፈሊጥና የኑሮ መልክ ሊጋለጥ ይችላል። አንደኛው እስኪያይል ወይም ሁለቱም እስኪዋሐዱ ድረስ የወትሮው እና የአሁኑ በሕሊና ውስጥ የባላንጣዎች ተቃርኖ ይፈትራሉ።

       እንዲህ ያለ ሰውነት ሲታገል ይቆይና ሲሰለቸው፦ የቸልተኘነት፣ የግዴለሽነት ኢንዲፈረንቲዝም መንፈስ ይሰፍንበታል። ይህ በተለይ የሚገለጸው በሥነ ምግባር መስክ ነው። ሥለታም የነበረው ሥነ ምግባራዊ በሕሊናው ይሰንፋል። የሚመቹ፣ የማይቆረቁሩ፣ የማይጋጩ እንደ ዘዴኝነት፣ ጮሌነት፣ ብልሃተኝነት፤ ያሉ የማይጨበጡ የቀልጣፋ ሰውነት ጠባዮች ያይላል።አስመሳይ፣ አድር ባይ፣ እንደ እምነቱ የማያምን፣ እንደ ኑሮው የማይኖር፣ የሕሊናውን ብኵርና ለምስር ንፍሮ የለወጠሌላም ሌላም። እንደ አለንጋ የሚጋረፉ ተግሣጾች ወቅታዊነታቸውን የሚያገኙት በዚህ ሳቢያ ይመስለናል።የሞራል ድቀትየሚባለው ይህ ሳይሆን ይቀራል? የመነሳቱ፣ የመቆሙ፣ ከራሱ ጋር ተስማምቶ ሚዛን ጠበቆ የመራከመዱ፤ ነገርስ እንዴት ይሆን? ቅን ሕሊና የማያልፈው ጥያቄ ነው።
                           +++++++++++++++++              +++++++++++++++++