Showing posts with label ለጥያቄዎ ምላሽ. Show all posts
Showing posts with label ለጥያቄዎ ምላሽ. Show all posts

Thursday, November 13, 2014

"ምስጢራዊ ቡድን" ክፍል ፪ በመምህር ምሕረትተአብ አሰፋ


(የደብረ መዊዕ /ሚካኤል / ስብከተ ወንጌል ሐላፊ

 በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁዋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ፥ ነገር ግን በየዋህነትና በፍርሃት ይሁን።” (፩ኛ ጴጥ ፫፥፲፭)

የዚህምስጢራዊ ቡድንየተሰኘው ትምህርታዊ ምላሽ ዓላማ፦ ከውጭ ኾነው፥ ቤተ ክርስቲያናችንን መዋጋት የተሳናቸው፣ እኛን አኽለውና እኛን መስለው ወደ ውስጣችን በመግባት፣ በዲቁናና በቅስና ከተቻለም እስከ ጵጵስና መሐረግ በመድረስ፣ ቀን ጠብቀውና ጊዜ አመቻችተው፣ ጸረ-ክርስትናን የኾነን እምነት እንደ አዲስ እንደተቀበሉ በማወጅ፣ የእምነቱ ተከታይዎች ላይ ጥርጣሬ በመዝራትና ከተቻለም አስክዶ በመውሰድ፤ ጸረ-ክርስትናን እንቅስቃሴ የሚያደርጉትን ወገኖች ማጋለጥ ሲሆን፤ በሌላ መልኩ፥ እነዚህ ጸረ-ቤተ ክርስቲያ ኃይሎች የዘሩትን የኑፋቄ ትምህርት ሰምተው፣ ግራ የተጋቡ አማንያንን ለማረጋጋትና የያዙት እምነት እውነተኛ የሕይወት መንገድ መሆኑን፣ ቤተ ክርስቲያንም፥ ለሚጠይቋት ሁሉ በቂና ከበቂ በላይ የኾነ መልስ እንዳላት ለማስገንዘብ ነው።

ከዚህ በፊት (በምስጢራዊ ቡድን በክፍል እና በማፈናጠር ይመልከቱ) እንደገለጽነው አንድ ሠው የፈለገውን እምነት እንዲያምንና ያመነበትን እምነት እንዲከተል ሕገ-መንግሥታዊም ሆነ ሕገ-እግዚአብሔራዊ ነፃነት እንዳለው ቢታወቅም፤ የራስን እምነት፥ በነፃነት ማራመድ፣ ያወቁትን ለራስ እምነት ተከታዮች ማሳወቅ እየተቻለ፤ የሌላውን እምነት፥ ማንቋሸሽና ማጥላላት፣ መለኮታዊ የሆኑትን ቅዱሳት መፃሕፍትን መንቀፍ፣ አማንያኑን መዝለፍ፤ ተገቢ ነው ብለን አናምንም!

መቼም ዛፍ እራሱን ለመከላከል ካልሆነ በቀር መኪና ገጭቶ አያውቅም እንደተባለ፤ ሳንደርስባቸው ለደረሱብን፣ ሳንነካቸው ለነኩን፤ ዶግማችንና ቀኖናችን እንዲሁም ሥርዓታችንን አልፎም ትውፊታችንን ለመናድ ለሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች እንደየ አመጣጣቸው ተገቢውን መልስ መስጠት ግድ ይለናል።

ሁኔታዎች አሳሳቢ እየሆኑ ነው፤ የተነገሩት ትንቢቶች በአፋጣኝ እየተፈጸሙ ነው። ወደድንም ጠላንም፥ አሁን የመጨረሻው መጨረሻ ላይ ነን።

ስለዚህ በአፋጣኝ ይህንን ቪሲዲ ይመልከቱና ላላዩት በማሳየት ክርስቲናዊ ግዴታዎን ይወጡ።
 
የኻሊድ ካሳሁንና የዳኢ ኻሊድ ክብሮም የተዛባ  አስተምህሮታቸውንና እነርሱ ስተው፣ ሌላውን ለማሳት የተደረገውን ሴራ የሚያጋልጥ፣ ጥልቅና ድንቅ፣ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ፍቃድ አጋዥነት ምጡቅ ምላሽ በወንድማችንና በመምህራችን በመምህ ምሕረትተአብ አሰፋ የተዘጋጀ ምስለ-ወድምፅ (ቪሲዲ) ይመልከቱና ላላዩት በማሳየት ክርስቲናዊ ግዴታዎን ይወጡ!


 

  ቀጣዩን፥ "ምስጢራዊው ቡድን" ክፍል ፪/ለን ይህን በማፈናጠር ይመልከቱ!


Sunday, April 20, 2014

ክርስቶስ፥ በከርሰ መቃብር፤ ሦስት መአልት ሦስት ሌሊት እንዴት ሊሞላው ቻለ? በቀሲስ ብርሃኑ ጎበና

        ክርስቶስ ሦስት መአልት ሦስት ሌሊት፣ በከርሰ መቃብር አደረ፤ የሚባለው፥ እንዴት ሆኖ ነው? (ለሚለው ጥያቄ፥ ምላሹ በሁለት ዓይነት አረዳድ እንገነዘባለን)

        
፩፤ ለዚህ ምላሽ የዕብራውያንን አቆጣጠር ማወቅ ያስፈልጋል:: የመጽሐፍ ቅዱስን ምስጢር ለማወቅ መጽሐፍ ቅዱስን የጻፉት የዕብራውያንን ሥርዓት ወግና ጂኦግራፊያዊ (መልክአ ምድራዊ) አቀማመጥ ያስፈልጋል።

        
ምክያቱም፥ ጸሐፊዎቹ ባህላቸውንና ሥርዓታቸውን ጠብቀው የጻፉት ስለሆነ ነው። ጌታ ዓርብ ተሰቅሎ ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ ከተነሳሣ እንዴት ብሎ ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት ይሞላል ሊያሰኝ ይችላል።

        
ዕብራውያንን አቆጣጠር ሌሊት የሚቆጠርው በዋዜማው ካለው አሥራ አንድ ሰዓት ጀምሮ ነው። ከአሥራ አንዱ ሰዓት በፊት ያሉት ሰዓቶች ግን አንድ ሰዓትም ቢሆን እንደ አንድ መዓልትና ሌሊት ይቆጠራል። ጌታ የተቀበረው ዓርብ ከአሥራ አንድ ሰዓት በፊት ስለሆነ የተቀበረበት ሰዓት የዓርብን መዓልትና ሌሊት ያጠቃልላል።

        
አርብ ከሠርክ አሥራ አንድ ሰዓት ጀምሮ እስከ ቅዳሜ አሥራ አንድ ሰዓት ከሰዓት በዋላ ድረስ ያለው የቅዳሜ መዓልትና ሌሊት ነው። ቅዳሜ ከአሥራ አንድ ሰዓት ጀምሮ ያለው እሑድ ነው። አንዱም ሰዓት ቢሆን ከላይ እንደ ተገለጠው የዕለቱን ሰዓቶችን ያሟላል። ጌታም የተነሣው እሑድ በመንፈቀ ሌሊት ስለሆነ ሦስት መዓልት ሶስት ሌሊት ይሆናል።

        
፪፤ ሁለተኛው ደግሞ የተሰቀልው በዕለተ አርብ ሰለሆነና የሞተውም በዕለት አርብ በመሆኑ አቆጣጠሩ ከአርብ ጠዋት ይጀምራል። አርብ ጠዋት ከ፲፪ ሰዓት እስከ ሰዓት ድረስ በምድር ላይ ብርሃን ነበር፤ አንድ ቀን።

        
ከ፮ እስከ ሰዓት በምድር ላይ ጨለማ ሆነ ይላል መጽሐፍ ቅዱስ፤ ያም፥ ጨለማ እውነተኛ ጨለማ እንጂ በምትሐት የሆነ ስላልሆነ እንደ ሌሊት ይቆጠራል። አንድ ቀን አንድ ሌሊት ይኖረናል። አርብ ከ፱ ሰዓት እስከ ምሽቱ ፲፪ ሰዓት እንደገና ቀን ሆኖአል፤ አርብ ሌሊት ለቅዳሜ አጥቢያ ያለውን ጨለማ ወይም ሌሊት ስንቆጥር ሁለት ቀን ሁለት ሌሊት ይሆናል።

        
ቅዳሜ ሙሉ ቀንና ሌሊት ለእሁድ አጥቢያ ጌታ እሁድ ሌሊት ተነስቷል፤ አንድ ላይ ሲደመር ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት ይሆናል። እንግዲህ በሁለቱም ዓይነት የሚቆጥሩ ስላሉ ሁለቱም ዓይነቶች ቀርበዋል እኛም የገባንና የተረዳንን አቆጣጠር መርጠን ማስረዳትም መረዳትም እንችላለን።

                     
<<<<<<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! >>>>>>>>

ምንጭ፦ ዓምደ ሃይማኖት /ገፅ ፹፱/ ሲስ ብርሃኑ በና