Tuesday, April 30, 2013

"ሰሙነ ሕማማት" በዲያቆን ኅብረት የሺጥላ


         ‹‹ሰሙነ ሕማማት›› መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥርዓት ነው፡፡ በርካታ ሰዎች ቤተ ክርስቲያንን ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ የምትጓዝ አካል አድርገው ሊገልጧት ይሞክራሉ፡፡ ይህ እጅግ አላዋቂ መሆናቸውን ይመሰክራል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ከመጽሐፍ ቅዱስ ያልተገኘና በሥጋዊና በደማዊ ዕውቀት ላይ የተመሠረተ ሥርዓት የላትም፡፡ ቅዱስ ሉቃስ በሐዋርያት ሥራ ‹‹ከሕማማቱ በኋላ›› በማለት ስለ ሰሙነ ሕማማት የሚያወሳ ቃል ተጠቅሟል፡፡ (የሐዋ1.3)

            ሰሙነ ሕማማት የሁለት ቃላት ጥምር ውጤት ነው፡፡ ‹‹ሰሙን›› የሚለው ቃል ‹‹ሰመነ›› ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ስምንት ቀኖች ወይም ሳምንት ማለት ው፡፡ ‹‹ሕማማት›› የሚለው ቃልም እንደዚሁ ‹‹ሐመመ›› ወይም ‹‹ሐመ›› ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን መከራዎች ማለት ነው፡፡ ‹‹ሕማማት›› የምንለው ለብዙ ሲሆን ነው፡፡ ለአንድ ወይም ለነጠላ ሲሆን ደግሞ ‹‹ሕማም›› እንላለን፡፡ እንግዲህ ሁለቱን ቃላት በማናበብ ‹‹ሰሙነ ሕማማት›› ስንል ‹‹የመከራዎች ሳምንት›› ማለታችን ነው፡፡

Thursday, April 25, 2013

“ምስጢራዊው ቡድን”

 በመምህር ምሕረትተአብ አሰፋ (የደብረ መዊዕ ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ስብከተ ወንጌል ሐላፊ)

“በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁዋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ፥ ነገር ግን በየዋህነትና በፍርሃት ይሁን።” 1ኛ ጴጥ 3፥15
 

     በዚህ “ምስጢራዊው ቡድን” በተሰኘው ቪሲዲ ትምህርታችን የምንመለከተው በተዋህዶ ጓዳ በክርስትና ዓለም ምሽጋቸውን መሽገው በዲቁናና በቅስና እንዲሁም በምንኩስና ከተቻላቸውም በጵጵስና መሐረግ በየአብያተ ክርስቲያናቱና በየገዳማቱ ተደብቅው ከቆዩ በኃላ ውስጣችን አጥንተው ምስጢራችንን አየተው የስለላ ስራቸውን በማጠናከር ቀን ጠብቅው ጊዜ አመቻችተው እኛ ኮብልለናል እናንተም ኮብልሉ በማለት እንጀራችንን በልተው ተረከዛቸውን በኛ ላይ ስለሚያነሱብን ወገኖች ነው።

        ሃያ ሰባት ዓመት በክርስትናው ዓለም ቆይቻለሁ፥ ክርስትናንም ከእግር እስከ ራሱ መርምርያለሁ ነገር ግን የሚያሳምነኝ ነገር ለህሊናዬ አላገኘሁም በማለት፦ “ጉዞ ወደ ኢስላም” በሚል የኮበለለውን በእንጦንስና በመቃርስ ቆብ የቆመረውን የትላንቱን አባ ወ/ሥላሴ የዛሬው ኻሊድ ካሳሁንን ምስጢራዊ ተልዕኮ መርምረን ላነሳቸው ጥቄዎች መልስ የምንሰጥ ሲሆን በቀጣይነት ልክ እንደ ኻሊድ ካሳሁን “ብርሀናዊው ጎዳና” በማለት የክርስትናውን ዓለምና ክርስትናን በማጠልሸት ለኮበለለው ዳኢ ኻሊድ ክብሮም መልስ የምንሰጥ ይሆናል።

               ከሁሉ አስቀድመን ማስተዋል ያለብን ነገር ቢኖር ሠው የፈለገውንና የመረጠውን እንዲሁም ያመነበትን ማምለክ እንደሚችል ሕገ እግዚአብሔርም ሆነ ሕገ መንግስት በሚገባ ደንግገውታል። ነገር ግን ሠው ከራሱ አልፎ ሌላው ያዋጣኛል ብሎ ያመነበትን ማንቋሸሽና ማጠልሸት ተገቢ ነው ብለን አናምንም።