Sunday, November 30, 2014

መጀመሪያ ሰው ነኝ (ሙሐዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት)



አንድ ወዳጄ በየገጸ ድሩና በየውይይት መድረኩ የሚሰማውንመጀመሪያ ኦሮሞ ነኝ፣ መጀመሪያ ትግሬ ነኝ፣ መጀመሪያ አማራ ነኝየሚል ክርክር አየናአንተ መጀመሪያ ምድንነህ?›› ሲል ጠየቀኝ፡፡
 
እኔ መጀመሪያ ሰው ነኝ፡፡ የተፈጠርኩትም ሰው ሆኜ ነው፡፡ አምላክም የፈጠረው ሰውን ነው፡፡ ቡድን፣ ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ ጎሳ፣ ነገድ የሚባሉ ነገሮችን ፈጠረ የሚል መጽሐፍም ትምህርትም አላገኘሁም፡፡ ክብርም፣ ሥልጣንም፣ ጥበብም፣ ፈጣሪውን መምሰልም የተሰጠው ለሰው ነው፡፡ መላእክት ሲፈጠሩ በማኅበር ነው የተፈጠሩት፡፡ አንድ ላይ ነው የተገኙት፡፡ ሰው ግን ሲፈጠር በየተራ ነው፡፡ መጀመሪያ አዳም፣ ከዚያ ሔዋን፣ ከዚያ ቃየል፣ ከዚያ አቤል እያለ ተራ በተራ፡፡ ቡድኖቹን ሰው በኋላ ራሱ ፈጠራቸው እንጂ አብረውት አልተፈጠሩም፡፡

መጀመሪያ ሰውነቴ ነበረ በኋላ ቡድኔ መጣ፡፡ በኋላ የመጣው ቡድኔ በፊት የነበረውን ሰውነቴን ከዚህ አትለፍ ከዚህ አትውጣ፣ ከዚህ አትዝለል ከዚህ አትሻገር አለው፡፡ ቡድኔ በእኔ መጠራት ሲገባው እኔ በቡድኔ ተጠራሁ፡፡ ለእርሱ ህልውና ሲል እኔን ሰዋኝ፡፡ እርሱ ሳይመጣ በፊት ግን እኔ ሰውዬው ነበርኩ፡፡

መጀመሪያ ሰው ስለነበርኩ መጀመሪያ ሰው ነው መከበር ያለበት፣ መጀመሪያ ሰውነቴ ነው መብት የሚያስፈልገው፣ ሰውነቴን አሥረህ፣ ገርፈህ፣ ገድለህ፣ ነጥቀህ፣ ቀምተህ ቡድኔን ከየት ታገኘዋለህ? እኔን ትተህ እንዴት እኔ ለፈጠርኩት ቅድሚያ ትሰጣለህ? እኔን ንቀህ እንዴት እኔነት ተሰባስቦ ላቋቋመው ቡድን ክብር ትሰጣለህ? ይኼማ ሐሰት ነው፡፡ ሴሎቹን ገድለህ ሰውየውን ማኖር ትችላለህ? ገጾቹን ገንጥለህስ መጽሐፉን ታኖራለህን? ከብቶቹን አርደህ ስለ መንጋው መጨነቅስ ምን ማለት ነው?

Sunday, November 23, 2014

መልካምና ክፉ ልጅ


   በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ሜን!


ልጅህ፥ ክፉ ከሆነ፦

* እንደ ቃየል በቅናት ካደገ የገዛ ወንድሙን ይገድላል። (ዘፍ ፬፥፭)

* እንደ ካም ካደገ ያንተኑ ሃፍረት ይገልጥብሃል። (ዘፍ ፱፥፳፩-፳፪)

* እንደ ዲና ካደገች ሂዳ ከጠላቶችህ ትወዳጃለች። (ዘፍ ፴፬፥፩)

* እንደ ዔሳው ካደገ ምቀኛ ይሆንብሃል። (ዘፍ ፲፯፥፵፩-፵፭)

* እንደ ይሁዳ ልጆች ካደገ የከፋ ይሆንብሃል። (ዘፍ ፴፰፥፩-፲፩)

* እንደ ሮቤል ካደገ ሚስትህን ይቀማሃል። (ኩፍ ፳፰፥፴፭-፵፬)

* እንደ አፍኒንና ፊንሐስ ካደገ ታቦት ሻጭ ይሆንብሃል። (፩ኛ ሳሙ፪፥፲፪)

* እንደ አምኖን ከደገ የገዛ ኅህቱን ይደፍርብሃል። /፪ኛ ሳሙ ፲፫፥፩-፲፱)

* አንደ አቤሴሎም ካደገ አንተንም ያሳድድሃል። (፪ኛ ሳሙ ፲፯፥፳፩-፳፬)

ልጅህ፥ መልካም ከሆነ፦ 

* አንደ ሴምና ያፌት ካደገ ሃፍረትህን ይደብቅልሃል። (ዘፍ ፱፥፳፫)

* አንደ ዮሴፍ ካደገ በችግርህ ደራሽ ይሆንልሃል። (ዘፍ ፴፱፥፯-፳፫)

* እንደ ይስሐቅ ካደገ ታማኝ ሆኖ ራሱን ይሰዋል። (ዘፍ ፳፪፥፱)

* እንደ ሳሙኤል ካደገ የእግዚአብሔር ሰው ይሆንልሃል። /፩ኛ ሳሙ ፫፥፲፯-)

* እንደ ዳዊት ካደገ የአገርህን ጠላት ያጠፋልሃል፤ በሰውም በእግዚአብሔር ፊት የተወደደ ይሆንልሃል። /፩ኛ ሳሙ ፲፯፥፴፬-፶፬)

"ልጆች ኖሩህ (በክርስቶስ ፍቅር) ምከራቸው፤ ከሕፃንነታቸው ጀምረህ ትሕትናን አስተምራቸው።" (ሲራ ፯፥፳፫)

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ክብር ለድንግል ማርያም!

ምንጭ፦ ዛክ ኢትዮጵያ

Thursday, November 13, 2014

"ምስጢራዊ ቡድን" ክፍል ፪ በመምህር ምሕረትተአብ አሰፋ


(የደብረ መዊዕ /ሚካኤል / ስብከተ ወንጌል ሐላፊ

 በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁዋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ፥ ነገር ግን በየዋህነትና በፍርሃት ይሁን።” (፩ኛ ጴጥ ፫፥፲፭)

የዚህምስጢራዊ ቡድንየተሰኘው ትምህርታዊ ምላሽ ዓላማ፦ ከውጭ ኾነው፥ ቤተ ክርስቲያናችንን መዋጋት የተሳናቸው፣ እኛን አኽለውና እኛን መስለው ወደ ውስጣችን በመግባት፣ በዲቁናና በቅስና ከተቻለም እስከ ጵጵስና መሐረግ በመድረስ፣ ቀን ጠብቀውና ጊዜ አመቻችተው፣ ጸረ-ክርስትናን የኾነን እምነት እንደ አዲስ እንደተቀበሉ በማወጅ፣ የእምነቱ ተከታይዎች ላይ ጥርጣሬ በመዝራትና ከተቻለም አስክዶ በመውሰድ፤ ጸረ-ክርስትናን እንቅስቃሴ የሚያደርጉትን ወገኖች ማጋለጥ ሲሆን፤ በሌላ መልኩ፥ እነዚህ ጸረ-ቤተ ክርስቲያ ኃይሎች የዘሩትን የኑፋቄ ትምህርት ሰምተው፣ ግራ የተጋቡ አማንያንን ለማረጋጋትና የያዙት እምነት እውነተኛ የሕይወት መንገድ መሆኑን፣ ቤተ ክርስቲያንም፥ ለሚጠይቋት ሁሉ በቂና ከበቂ በላይ የኾነ መልስ እንዳላት ለማስገንዘብ ነው።

ከዚህ በፊት (በምስጢራዊ ቡድን በክፍል እና በማፈናጠር ይመልከቱ) እንደገለጽነው አንድ ሠው የፈለገውን እምነት እንዲያምንና ያመነበትን እምነት እንዲከተል ሕገ-መንግሥታዊም ሆነ ሕገ-እግዚአብሔራዊ ነፃነት እንዳለው ቢታወቅም፤ የራስን እምነት፥ በነፃነት ማራመድ፣ ያወቁትን ለራስ እምነት ተከታዮች ማሳወቅ እየተቻለ፤ የሌላውን እምነት፥ ማንቋሸሽና ማጥላላት፣ መለኮታዊ የሆኑትን ቅዱሳት መፃሕፍትን መንቀፍ፣ አማንያኑን መዝለፍ፤ ተገቢ ነው ብለን አናምንም!

መቼም ዛፍ እራሱን ለመከላከል ካልሆነ በቀር መኪና ገጭቶ አያውቅም እንደተባለ፤ ሳንደርስባቸው ለደረሱብን፣ ሳንነካቸው ለነኩን፤ ዶግማችንና ቀኖናችን እንዲሁም ሥርዓታችንን አልፎም ትውፊታችንን ለመናድ ለሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች እንደየ አመጣጣቸው ተገቢውን መልስ መስጠት ግድ ይለናል።

ሁኔታዎች አሳሳቢ እየሆኑ ነው፤ የተነገሩት ትንቢቶች በአፋጣኝ እየተፈጸሙ ነው። ወደድንም ጠላንም፥ አሁን የመጨረሻው መጨረሻ ላይ ነን።

ስለዚህ በአፋጣኝ ይህንን ቪሲዲ ይመልከቱና ላላዩት በማሳየት ክርስቲናዊ ግዴታዎን ይወጡ።
 
የኻሊድ ካሳሁንና የዳኢ ኻሊድ ክብሮም የተዛባ  አስተምህሮታቸውንና እነርሱ ስተው፣ ሌላውን ለማሳት የተደረገውን ሴራ የሚያጋልጥ፣ ጥልቅና ድንቅ፣ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ፍቃድ አጋዥነት ምጡቅ ምላሽ በወንድማችንና በመምህራችን በመምህ ምሕረትተአብ አሰፋ የተዘጋጀ ምስለ-ወድምፅ (ቪሲዲ) ይመልከቱና ላላዩት በማሳየት ክርስቲናዊ ግዴታዎን ይወጡ!


 

  ቀጣዩን፥ "ምስጢራዊው ቡድን" ክፍል ፪/ለን ይህን በማፈናጠር ይመልከቱ!