Sunday, August 24, 2014

“ጆሮዬም ሹክሹክታውን ሰማች” (ኢዮ ፬፥፲፪)


ይኼንን ርዕስ የተናገረ  “ጆሮዬም ሹክሹክታውን ሰማች” ያለ ፃድቁ ው። ፃድቁ ብ በክፉ በሽታና በጽኑ በተከዘ ጊዜ፥  ሦስቱም የኢዮብ ወዳጆች የደረሰበትን ክፉ ነገር ሁሉ ሰምተው ሊያዝኑለትና ሊያጽናኑት እንደመጡ ታላጽሐፍ ቅዱስ ይተርክልናልም፣ ተጽፎም እናነባለን

ቢኾንም ግን ሦስቱም የኢዮብ ወዳጆች በትንሹ ሐዘኑን ሊጋሩት ሞከሩ፣ ነገር ግን እስከ-መጨረሻው ሐዘኑን ሊጋሩት አልሉም። የኢዮብን፥ ሐዘኑን ሊጋሩት የመጡት ሰዎች እንኳን ከልባቸው ሊያዝኑለት ይቅና ሌላ የሐዘን ቁስል እንደጨመሩበት፣ ከማጽናናትም ይልቅ፥ እንዳይጽና በቁስሉ ቁስል ጨመሩበት፣  የኢዮብን፥ ብርታቱንና የጥንካሬውን እንዲሁም የፈሪሐ-እግዚአብሔሩን ውጤት ፍሬ-አልባ ለማስመሰል ያደረጉት ጥረት በፃድቁ ብ ዘንድ ዋጋ የለውም ነበር። ሦስቱ የኢዮብ ወዳጆቹ ከንቱ ውትወታ፤ በፃድቁ ኢዮብ ዕይታ ሲታዩ እንዲህ ይገልፆቸዋል፦ "ለእኔም በምሥጢር ቃል መጣልኝ፥ ጆሮዬም ሹክሹክታውን ሰማች" ይላቸዋል።

በምሥጢር ቃል ማምጣታቸውና ጆሮውም ሹክሹክታቸውን መስማቱ፤ ለመጣበት ፈተና በብቃት ማለፍና ለመንፈሳዊ ተጋድሎውና ለሕይወቱ መቅረዝ እንዳደረገው እንመለከታለ። ወደ ታች ወረድ ሲል ደግሞ “የዝምታ ድምጽ ሰማሁ” ይላል። (ኢዮ ፬፥፲፮)

በዝምታ ድምጽ ውስጥ ብዙ መልእክት አለ! ነቢየ ኤልያስም በዝምታ ድምጽ ውስጥ ነበር እግዚአብሔር የተገለጠለት። እነሆም፦ “በእግዚአብሔርም ፊት ትልቅና ብርቱ ነፋስ ተራሮቹን ሰነጠቀ፣ ዓለቶቹንም ሰባበረ፥ እግዚአብሔር ግን በነፋሱ ውስጥ አልነበረም። ከነፋሱም በኋላ የምድር መናወጥ ሆነ፥ እግዚአብሔር ግን በምድር መናወጥ ውስጥ አልነበረም። ከምድር መናወጥ በኋላም እሳት ሆነ፥ እግዚአብሔር ግን በእሳቱ ውስጥም አልነበረም። ከእሳቱም በኋላ፥ ትንሽ የዝምታ ድምፅ ሆነ። በዚ በዝምታ ድምፅ ነበር የእግዚአብሔር ድምጽ የተሰማው። (፩ኛ ነገ ፲፱፥፲፪)

Tuesday, August 19, 2014

ከፕሮፌሰራችን ዕይታ፦ የማልስማማበት



ፕሮፌሰራችን መስፍን ወልደ ማርያም ለሃገራችን፣ ለሕዝባችን፣ ለሀሕጉራችን፤ ትልቅ አስተዋጽዎ ካበረከቱ አንዱ ምርጥ ኢትዮጵያዊ ናቸው። ስለ ፕሮፍ አጠቃላይ ስለሰሩት መልካም ስራዎች፣ ስላበረከቱት ታላቅ አስተዋጽዎ በዚች አነስተኛ ጹሑፍ ለመዘከር አይደለም፤ ይልቅ የፕሮፋችን ዕይታ፣ ተመክሮ፣ ልምድ፣ ሕይወት፤ በዚህ ባሳለፍነው ተከታታይ አምስት ሳምንታት ከምንወዳትና ከምናከብራት፥ ከመዓዛ ብሩ ጋር እያደረጉት ያለውን ቃለ-መጠይቅ እያዳመጥናቸው ነው።

ሦስት ነገስታንን በሕይዎታች የተመለከቱ እኚህ ፕሮፋችን፥ በንግግራቸውም ረጋ ያሉና አንደበተ ርዕቱ ናቸው፣ እጅግ ማራኪ በኾነ አገላለጽ ታሪኮችን ያማክላሉ፣ የራቀውን አቅርበው እያጣጣሙ እያስቃኙን ነው። ቢኾንም ከፕሮፌሰራችን ዕይታዎቻና ቅኝቶች፦ የማልስማማበት ነገሮች ቢኖሩም፤ ከማልስማማበት አንዱ ደግሞ “የመንፈሳዊ ልዕልና” ብለው በዘረዘሩት ውስጥ “የቱ ጳጳስ፣ የቱ ቄስ ነው? ድኾች ተጠቅተዋል፣ ፍትሕ ጎደለ፣ ሠው ተበደለ ብሎ የጮ። የለም!። ካሉ በኋላ በእርሶ ጊዜ፦ አቡነ ባስልዮስ፥ ከንጉስ እጅ እርስዎና ከእርስዎ ጋር ሊገረፉ የነበሩትን ሠዎች ስለታደጉ ብቻ “ከአቡነ ባስልዮስ በኋላ ማንም!” የለም ማለትዎን ስለማልቀበለው ከአቡነ ባስልዮስ በኋላ፦ ድኾች ተጠቅተዋል፣ ፍትሕ ጎደለ፣ ሠው ተበደለ ብው የጮኹ አሉ!፤  ለዚህም  ከታች ያለውን አነስተኛ ጹሑፍ ላዘጋጅ ወደድሁኝ። እንደ መረጃና እንደ-ማስረጃ ይኾነን ዘንድ እንሆ ኹለቱን፦

Sunday, August 10, 2014

የሁላችንም ሐሳብ



         በቅንነት፥ ብንነጋገርና ብንሠራ፣ የሁላችንም ሐሳብ ለኢትዮጵያ ይጠቅማል እንጂ አይጐዳም!”  (ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ)