Sunday, August 24, 2014

“ጆሮዬም ሹክሹክታውን ሰማች” (ኢዮ ፬፥፲፪)


ይኼንን ርዕስ የተናገረ  “ጆሮዬም ሹክሹክታውን ሰማች” ያለ ፃድቁ ው። ፃድቁ ብ በክፉ በሽታና በጽኑ በተከዘ ጊዜ፥  ሦስቱም የኢዮብ ወዳጆች የደረሰበትን ክፉ ነገር ሁሉ ሰምተው ሊያዝኑለትና ሊያጽናኑት እንደመጡ ታላጽሐፍ ቅዱስ ይተርክልናልም፣ ተጽፎም እናነባለን

ቢኾንም ግን ሦስቱም የኢዮብ ወዳጆች በትንሹ ሐዘኑን ሊጋሩት ሞከሩ፣ ነገር ግን እስከ-መጨረሻው ሐዘኑን ሊጋሩት አልሉም። የኢዮብን፥ ሐዘኑን ሊጋሩት የመጡት ሰዎች እንኳን ከልባቸው ሊያዝኑለት ይቅና ሌላ የሐዘን ቁስል እንደጨመሩበት፣ ከማጽናናትም ይልቅ፥ እንዳይጽና በቁስሉ ቁስል ጨመሩበት፣  የኢዮብን፥ ብርታቱንና የጥንካሬውን እንዲሁም የፈሪሐ-እግዚአብሔሩን ውጤት ፍሬ-አልባ ለማስመሰል ያደረጉት ጥረት በፃድቁ ብ ዘንድ ዋጋ የለውም ነበር። ሦስቱ የኢዮብ ወዳጆቹ ከንቱ ውትወታ፤ በፃድቁ ኢዮብ ዕይታ ሲታዩ እንዲህ ይገልፆቸዋል፦ "ለእኔም በምሥጢር ቃል መጣልኝ፥ ጆሮዬም ሹክሹክታውን ሰማች" ይላቸዋል።

በምሥጢር ቃል ማምጣታቸውና ጆሮውም ሹክሹክታቸውን መስማቱ፤ ለመጣበት ፈተና በብቃት ማለፍና ለመንፈሳዊ ተጋድሎውና ለሕይወቱ መቅረዝ እንዳደረገው እንመለከታለ። ወደ ታች ወረድ ሲል ደግሞ “የዝምታ ድምጽ ሰማሁ” ይላል። (ኢዮ ፬፥፲፮)

በዝምታ ድምጽ ውስጥ ብዙ መልእክት አለ! ነቢየ ኤልያስም በዝምታ ድምጽ ውስጥ ነበር እግዚአብሔር የተገለጠለት። እነሆም፦ “በእግዚአብሔርም ፊት ትልቅና ብርቱ ነፋስ ተራሮቹን ሰነጠቀ፣ ዓለቶቹንም ሰባበረ፥ እግዚአብሔር ግን በነፋሱ ውስጥ አልነበረም። ከነፋሱም በኋላ የምድር መናወጥ ሆነ፥ እግዚአብሔር ግን በምድር መናወጥ ውስጥ አልነበረም። ከምድር መናወጥ በኋላም እሳት ሆነ፥ እግዚአብሔር ግን በእሳቱ ውስጥም አልነበረም። ከእሳቱም በኋላ፥ ትንሽ የዝምታ ድምፅ ሆነ። በዚ በዝምታ ድምፅ ነበር የእግዚአብሔር ድምጽ የተሰማው። (፩ኛ ነገ ፲፱፥፲፪)

ከሃገራችን ኢትያ መንግስትበዓለም ሃገራት መንግስታት ላይ  ጆሮዎቻችን ሹክሹክታውን የሰማች ነው፤ እነዚህ መንግስታት በትረ-መንግስታቸውን እንደጨበጡ ሃገሪቷን ትንሹ ከሐዘ ሊጋሩት ሞከሩ፣ ነገር ግን እስከ-መጨረሻው ሐዘን ሊጋሩት አልሉም፤ ለዚህም ነው እንደ ኢዮብ ወዳጆች ላ በቁስል ቁስል ያደረሉት። ቅሉ ግን ቃተ-ሕሊና ያለ ሃገ ወዳ ሕዝብና ነገሮቹንአርምመለከታል፤ ሕዝብም ልክ እንፃድቁ ብም "ለእኔም በምሥጢር ቃል መጣልኝ፥ ጆሮዬም ሹክሹክታውን ሰማች" ያለ በትዝብትና በቅን ከታተላቸዋል። 

ርሱ ግን (መንግስ) ራሳቸውንዚህሯት ሕዝብና አንድ ሃገር አሳቢና ተቆርቋሪ በማስመሰል፣ ሌሎች ለሃገራችን እንቆረቆራለን፣ ለሕዝባችን ይገደናል፤ የሚሉትን የሕብረ-ተሰእቡን ቅን አስተዋጽዎ የሚያበረክቱትን ግለሰቦችንና ድርጅቶችን ማዋከብና ሕዝብም ለሃገሪቷ የዕውቀት ምንጭና ንቃተ-ሕሊናውን እንዳይኖረው ለመገደብ በሥም ላይ ሌላ ሥም፣ በሕግ ላይ ሌላ ሕግ እያረቀቁና እያወጡ፤ የሕዝቡን በክፉ በሽታና በጽኑ መተከዘ (ነፃነቱን ሲነፍጉትና  ሕሊናው ሲገደብበት) ግድ አይላቸውም።

ዚህም የዓለማት ነገሥታት፥ የሕዝባቸውን መሠረታዊ ጥያቄ መመለስ ሲያቅታቸውና በሠላም ማስተዳደር ሲሳናቸው የሚወስዱት እርምጃ፦ ሕዝብሕዝብ በነቆራና በላቻ እንዲተያግ፣ ሕዝቡ ነፃነቱን ተጠቅሞ ከመናገርና ከመፃፍ እንዲቆጠብ ማድረግ፣ ለሚመጣው ትውልድ ዕቅድና ንድፍ ያለው ሠላማዊ ሃገር ከማስረከብ ይልቅ እነርሱ እስካሉ ድረስ ብቻ ሃገር እንደሚኖር መለፍለፍ ዋና ዋና ዓላማቸው ነው።

ይኼም አልበቃ ካላቸውም ምድርን በሚያናውጽ፣ ተራራዎችን በሚያንቀጠቅጥ፣ አለቶችን በሚሰነጣጥቅ፣ መትረየሶችንና ቦንቦች ይጠቀማሉ፤ በነዚህ፥ ምድርን በሚያናውጽ፣ ተራራዎችን በሚያንቀጠቅጥ፣ አለቶችን በሚሰነጣጥቅ፣ መትረየሶችንና ቦንቦችን መጠቀም ግን የተረጋገጠ ሠላምና ነ አይፍንምም፤ አይመጣም!። እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር ዳኛ (መንግስት) ሲኾኑ ደግሞ እንደ ሶርያ መንግሥትና ሕዝብ ይኾናሉ። (ሉቃ ፲፰፥፪) አምላክ ሆይ፦ከዚህስ ክፉና ጭካኔ ሠውረን!።

ሠላም ሊመጣ የሚችለው፦ መንግሥታት ይኹኑም የሃይማኖት መሪዎች፤ የሕዝባቸውን መሠረታዊ ጥያቄ በ"ዝምታ ድምፅ" ውስጥ ሰምተውና አዳምጠው (በአርምሞ፥ በጥልቀት አስበውና አሰላስለው) ሠላማዊ ምላሽ ሲሰጡ ብቻ ነው!።

ሕዝብ፥ ፍትሕ ከተጓደለበት፣ መብቱ ከተነፈገው፣ ከዓደባባይ ሠልፍ ይልቅ በሕሊናውና በልቡ ከታይታ ሠልፍ በላይ ያካሂዳል። ስለዚህም፦ "የሰው ብሶት በአንደበቱ ባይናገር ፊቱ፣ ኑሮው፣ ሕይወቱ ይናገራል። በዝምታ ይጮኻል። በዝምታ ያለቅሳል። በዝምታ አቤ….. ይላል።" (/ ኤፍሬም እሸቴ)

No comments:

Post a Comment