Showing posts with label ምልከታ. Show all posts
Showing posts with label ምልከታ. Show all posts

Wednesday, January 27, 2016

ይድረስ ለመንፈሳዊ መምህራኖቻችን (ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ)፦

       ውድ ወንድሞቻችንንና መምህራኖቻችን፥ ሠላምና ፍቅር በድንግል ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ከመላው ቤተሰባችሁ ጋር ይብዛላችሁ።

አንድ ነገር ለማለት ፈልጌ ነበር፥ እርሱም፦ <ለመንፈሳዊ ዝማሬ ዘመናዊ የሙዚቃ መሳሪያዎች ስለ መጠቀም> ጠቀሜታው ምንድን ነው? ጉዳቱስ እስከምን ያህል ነው? በሚል የግንዛቤ መስጫ ትምህርት እንዲሰጡን ከማሰብ የመነጨ ነው።

ምክንያቱም፦ እነ "ቀሲስ" ትዝታውና  እነ "ቀሲስ" መላኩ ሠሞኑን በፒያኖ (በኦርጋን) ስለመዘመር የሚያጣቅሱስ የዶክተር ኢሳያስና አለሜ ሥራዎችና አንዳንድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስር በፒያኖ (በኦርጋን) የዘመሩትን እንደነ ዘማሪ ኪነጥበብ፣ እንደነ ዘማሪ ይልማ ኃይሉ፣ እንደዘመሩ ይናገራሉ።

ነገር ግን ይህ እውነት በዚያን ጊዜ በፒያኖ (በኦርጋን) የተዘመሩ ዝማሬዎች በነባራዊው ኹናቴ ነው ወይንስ ለቤተክርስቲያን የመዝሙር ማሳሪያ ተደርጎ ለመንፈሳዊ ልዕልና፣ ለመንፈሳዊ አርምሞ የሚሰጠው ጠቀሜታ ታምኖበት ነው ወይ?

ይህንን አርዕስት በዋቢነት የሚጠቀሙት እነ "ቀሲስ" መላኩ ቢኾኑም ከዶክተር ኢሳያስ አለሜ ሃሳብ በመነሳት ነው፤ ይህም ሃሳብቸው እንዲህ ይላል፦ <ይኽውም የተደከመበት አጭር መዝሙረ ጸሎት የዜማው ስልት ለመሰንቆ፣ ለአርጋኖንና (ለኦርጋን) ለፒያኖ እንዲሁም ኖት ላላቸው የመዝሙር መሳሪያዎች ሁሉ ተስማሚ መሆኑን ለመዝሙር አፍቃሪዎቼ አስገነዝባለሁ> (መዝሙረ ጸሎት ገፅ /9 ዶክተር ኢሳያስ አለሜ የፃፉት) ይላል እንጂ በንጉሡም ይሁን በጊዜው የነበረ ቅዱስ ሲኖዶስ፦ በፒያኖ (በኦርጋን) ስለ መዘመር ስለ ጥቅሙና ስለ ጎጂንቱን አይገልፅም፣ አያብራራም!

የኾነው ኾኖ በእነ ዶክተር ኢሳያስ አለሜ ሃሳብ ተንተርሰው እየተከራከሩ ያሉት እነ "ቀሲስ" መላኩ  <የዜማው ስልት ለመሰንቆ፣ ለአርጋኖንና (ለኦርጋን) ለፒያኖ እንዲሁም ኖት ላላቸው የመዝሙር መሳሪያዎች ሁሉ> የሚለውን ጽንሰ ሃሳብ ምን ያህል በጥልቀት ተገንዝበውት ይሆን ወይ?

በእርግጥ በእነ ዶክተር ኢሳያስ አለሜ ሃሳብ ተንተርሰው እየተከራከሩ ያሉት እነ "ቀሲስ" መላኩ በዚሁ በፒያኖ (በኦርጋን) የሚያቆሙ አይመስሉም፣ ምክንያቱ፦ <ኖት ላላቸው የመዝሙር መሳሪያዎች ሁሉ> ያሉትን የዶክተር ኢሳያስን ጽንሰ ሃሳብ> በመያዝ ዛሬ በፒያኖ (በኦርጋን)  የተጀመረ ነገ ይቀጥልና ድረም፣ ሳክስፎን፣ ክላርኔት፣ ትራምሬት፣ ጊታር፣ ቫዮሊን ወዘተ . . .  እያሉ ይቀጥላሉ።

ስለዚህ <ለመንፈሳዊ ዝማሬ ዘመናዊ መሳሪያ> ስለ መጠቀም ስንነጋገር በሕዝብ ብዛትና በፐርሰንት ሳይኾን ለመንፈሳዊ አምልኮና ለመንፈሳዊ ዝማሬ አርምሞ (ተመስጦ) የቱ ነው ወደ መንፈሳዊ ልዕልና የሚመራን? መሠረታዊና ቀና መንፈሳዊ መንገድ የሚመራን የቱ ነው? በኦርጋን ወይንስ በክራር፣ በሳክስፎን ወይንስ በዋሽንት፣ ጃዝ ወይንስ ከበሮ፣ ቫዮሊን ወይስ ማሲንቆ፣ በኦርኬስትራ ሥነ ሥርዓት ላይ የሚይዙት ዘንግ ወይንስ መንፈሳዊ አባቶቻችን ለምስጋና የሚይዙት መቋሚያ፤ የቱ ነው ለመንፈሳዊ ዝማሬና ለአርምሞ (ለተመስጦ) የሚኾነው?

Saturday, January 16, 2016

ማሕበረ ቅዱሳን፥ ስምና ምግባሩ፦

ማ፦ ማገር ነው ለቤተክርስቲያናችን፤
ሕ፦ ሕይወተ ክርስቶስ መሰበኪያችን፤
በ፦ በረቱ ጥልቅ ነው መኖሪያችን፤
ረ፦ ረስተው አይሄዱም ታሪካችንን።

ቅ፦ ቅዱስ እግዚአብሔር አለ' በአንድነታቸው፤
ዱ፦ ዱካ ቅዱሳንን ተከትለው በሃይማታቸው፤
ሳ፦ ሳንቃውን ለሚያነቃንቁ እረፍት ይነሳሉ፤
ን፦ ንስጥሮሳዊያንን ተግተው ይዋጋሉ!።

(ስለ ማሕበረ ቅዱሳን ይህን እላለሁ፤ ስሙም ይኹን ምግባሩ በእኔ ገለፃ፦ ለቤተክርስቲያናችን ማሕበረ ቅዱሳን ማገር ነው!።)

Friday, October 2, 2015

በመልአከ መንክራት ግርማ ወንዱሙ ላይ ማጉረምረም ለምን? ክፍል ፫



በክፍል ሁለት ላይ ያቆምነው፦ «ስለ ከንቱ ውዳሴ እና ከከንቱ ውዳሴ ስለ ለማምለጥ» ነው፤ ካቆምንበት ስንቀጥል፦ እርግጥ ነው ማንኛውም ምዕመን ውዳሴ ከንቱ ከመስጡት መቆጠብ አለበት፣ እንዲሁም ደግሞ ማንኛውም መንፈሳዊ አገልጋይ ስለ መንፈሳዊ አገልግሎቱ ሲል ከውዳሴ ከንቱነት እራሱን መጠብቅ ግድ ይላል!፤ ይህ ታዲያ የሚሆነው በምዕመናን ዘንድ ይሁን በአገልጋዮች ዘንድ የመንፈሳዊነት ልዕልና ሲኖር ነው። በዚሁ «ስለ ከንቱ ውዳሴ እና ከከንቱ ውዳሴ ስለ ለማምለጥ» ስንነጋገር መምህር ግርማ፦ «እኔ አዳኝ አይደለሁም፥ ነኝ ብዬ ተናግሬ፣ ተመፃድቄም አላውቅም፤ አገልግሎት እየሰጠሁ እንጂ! የሚፈስና የሚያድው እግዚአብሔር አምልክ ነው!።» ያሉትን እናስታውስ።

ደግሞም ሁሉም መምህራን፥ ስለ መተተኞች፣ ስለ ጠንቋዮች፣ ስለ ድግምታሞች፣ ስለ ዛር መንፈሶች፣ አጠቃላይ ስለ አጋንት ሥራዎች መኖር ያውቃሉ፤ ስለነዚህ የአጋንት ሥራዎች እንዴት ማስቀረትና ፊቱን ወደ እግዚአብሔር ቤት እንዴት እንደሚመልስ በትምህርታቸው ውስጥ ይሰጣል፤ ቢሆንም ግን አሁን ስለምንነጋገርበት ወደ ጠንቋይና ወደ ቃልቻ ቤት የሚሄደንው፣ ሥራውን በመተትና በጥንቆላ የሚተዳደረውን ወደ እግዚአብሔር ቤት ፊቱን እንዲመልስ እያደረጉ ያሉትን አባት መምህር ግርማን መቃወም ምን የሚሉት ነገር ነው? ደግሞስ እኚሁ አባት፥ ካህናት መብላት ያለባችሁ ቅልጥም ጠንቋዩ እንዳይበላው፣ ካህናት መጠጣት የነበረባችው ጠጅ ጠንቋዩ  እንዳይጠጣው፣ ሕዝቡን እየሰኩ እያስቀሩ፣ ሕዝቡን ፍትፍቱን ወደ ጠንቋይ ቤት መውሰዱን እንዲያቆም እና ወደ ካህኑ እንዲያመጣው እያደረጉ ያሉ አባት ናቸው። ቤተ ክርስቲያንንም በማሳነጽ ረገድም የበኩላቸውን ድርሻ እያደረጉ ነው። እንደውም ስለ ቤተ ክርስቲያንን ማሳነጽ መጋቢ አእላፍ መክብብ አጥናው ያሉትን እናጢነው።

Sunday, May 17, 2015

“በፊቴም እረዱአቸው” (ሉቃ 19፥27) ምን ማለት ነው? በዲያቆን ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 6 ቀን 2007 /(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 6 ቀን 2007 ዓ/ም) )  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ስመ እግዚአብሔር ቀዳማዊ ዘእንበለ ትማልም፤ ወማዕከላዊ ዘእንበለ ዮም፤ ወደኃራዊ ዘእንበለ ጌሰም ፤ብሉየ መዋዕል ዘእንበለ ዓም፤ ፈጣሬ ኩሉ ዓለም ዘእንበለ ድካም፤ ባህረ ምሕረት ዘእንበለ አቅም፤ ብኁተ ሕሉና እስከ ለዓለመ ዓለም አሜን "ወባህቱ ለእልክቱሰ ጸላእትየ እለ ኢይፈቅዱ እንግሥ ላእሌሆሙ አምጽእዎሙ ዝየ ወርግዝዎሙ በቅድሜየ= ነገር ግን እነዚያን በላያቸው ልነግሥ ያልወደዱትን ጠላቶቼን ወደዚህ አምጡአቸው " /ሉቃ 1927/


መግቢያ
አንተ ደግሞ እርሱን እንዳትመስል ለሰነፍ እንደ ስንፍናው አትመልስለት።”(ምሳ 264)

ክርስትና ከሰብአዊነት ይልቃልመንፈሳዊነትም ከባለአእምሯዊነት ይበልጣልሃይማኖትም ከስሜት በላይ ነው

በቅርቡ ኢትዮጵያውያንና ግብጻውያን ቅዱሳን ሰማዕታተ ሊቢያ ላይ የተፈጸመውን ጭካኔ በተመለክተ ድርጊቱ የእምነቱን መርኅና የቁርአንን አስተምህሮ አይወክልም በሚል ዘውግ ከመሟገትና ከማውገዝ ይልቅ "መጽሐፍ ቅዱሳችሁም ቢሆን :- ነገር ግን እነዚያን በላያቸው ልነግሥ ያልወደዱትን ጠላቶቼን ወደዚህ አምጡአቸው በፊቴም እረዱአቸው። ይላል እኮ" በሚል ቅዱሱን ቃል ጠቅሶ ለመክሰስና ነቅሶ ለማርከስ የሚዳክሩ በዝተዋል:: እንኳን ቁርአኑ መጽሐፍ ቅዱሱም ቢሆን እንዲህ ይላል የሚለው

          አንደኛ ቁርአኑ እረዱ ግደሉ ይላል ብሎ ማመን ሲሆን ሁለተኛው የመጽሐፍ ቅዱስን ብልጫ ማመናቸውን ያሳየ ነው ለኛ ግን መጽሐፍ ቅዱስ ልክ ለመሆኑ ማረጋገጫችን የቁርአን ምስክርነት ወይም የሙስሊሞቹ ቃሉን ማጣቀስ አይደለም ይህንንም ፈጽሞ ከምስክርነትም የምናገባውና ጠቅሰውልናል ብለን የምናመሰግናቸው ዓይደለም:: በአንጻሩ የረከሰውን ሲቀድስና የበደለውን ሲወቅስ ማየቱ፤ በቅዱሳን መጻፉን ተፈትኖ ማለፉንመረዳቱ፤በአዝማናት ጅረት ማለፉንለትውልድ መትረፉን መመልከቱ ብቻ ለኛ አምኖ መቀበል አክብሮ መከተል በቂ ምክንያት ነው:: በስንፍናቸው ለሚኖሩ እንደድክመታቸውና በእነርሱ አመክንዮ ቁርአንማ እንዲህ ይላል እያሉ መመለስ ለቤተክርስቲያናችን የሚያቅት አይደለም ሆኖም ከስንፍናቸው ላለመተባበር የመጡበትንም የጥፋት መንገድ በመናቅ የቤተክርስቲያኒቱን ትምህርት ብቻ እንናገራለን:: ጠቢቡ እንዲህ ሲል እንደነገረን "አንተ ደግሞ እርሱን እንዳትመስል ለሰነፍ እንደ ስንፍናው አትመልስለት።" (ምሳ. 26:4) እንግዲህ በዓይነ ሥጋ እያነበበ በዓይነ ህሊና መረዳቱን ለሚሻ ግን በመጀመርያ ቃሉን አብራርቶ ከማስረዳትና ፈቶ ከመግለጥ በፊት የመጽሐፍ ቅዱስን መልእክት በምን መንገድ መረዳት እንደሚገባ ጥቂት ነጥቦች እናስቀምጥ

Monday, May 4, 2015

ጀማል ማነው? ሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት


ኤፍሬምና ጓደኞቹ

ጀማልየተባለ ሙስሊም ወንድማችን በሊቢያ ከተሠዉ ክርስቲያኖች ጋር አብሮ ተሠዉቷል እየተባለ ሲነገር ቆይቷልበአካባቢው የነበሩ የዓይን እማኞችና ሌሎችም የቅርብ ምንጮች ታሪኩ የተሳሳተ መሆኑን ቢናገሩም ሰሚ ለማግኘት ግን አልተቻለም፡፡ አንዳንዶቹም ታሪኩን የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች ፍቅር ማሳያ አድርገው ተሟግተዋል፡፡ እንደ እኔ ግን ይህንን ታላቅ ፍቅር ለማሳየትጀማልየተባለ መሥዋዕት መፍጠር አያስፈልገንም፡፡ ፍቅሩ ነበረ፤ አለ፡፡ ተጨማሪ ፈጠራው አያስፈልገውም ነበር፡፡

ኤፍሬም ሰማዕት ዘሊቢያ
ጀማልነው ተብሎ ሲነገርለት የነበረው ወንድማችን ግን ኤፍሬም የተባለ ኤርትራዊ፣ ቃኘው ሠፈር ይኖር የነበረ ክርስቲያን ነው፡፡ ቤተሰቦቹ ሁለት መርዶ እንደመጣባቸው እየገለጡ ነው፡፡ በአንድ በኩል በአሰቃቂ ሁኔታ በአይሲስ መሠዋቱ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞሙስሊምነው መባሉ ነው፡፡

      ኖርዌይ የነበሩ ኤርትራውያን ክርስቲያኖች ወዲያው ነበር ነገሩን የተቃወሙት፡፡ ነገር ግን አሥመራ ያሉት ቤተሰቦቹ እስኪረዱ ድረስ ትክክለኛ ስሙን ለመግለጥ አልተፈለገም፡፡ በዚህ መዘግየት የተነሣም ብዙ የፈጠራ ታሪኮች ተፈጠሩ፡፡

አንዳንድ የማኅበራዊ ሚዲያ አቀንቃኞች በላኩልኝ የውስጥ መልእክት የጀማልን ሙስሊምነት መካድ ሙስሊሞች ለክርስቲያኖች ያላቸውን ድጋፍና ፍቅር መካድ ነው ሲሉ ገልጠዋል፡፡ ለእኔ ግን ከተፈጠረውጀማልይልቅ እዚሁ አዲስ አበባ ያለው መሐመድ ካሣ ይህንን ልዩ ፍቅር ከንጋት ኮከብ በላይ አጉልቶ አሳይቶኛል፡፡ ልቡ እስኪደክም ኀዘንተኞቹን ለማጽናናትና ለመርዳት የሚደክመው፤ ለምን ጉባኤ አይደረግም፣ መዘምራን ለምን አይመጡም፣ መምህራን ለምን አያስተምሩም እያለ ልቅሶ ቤቶቹን ከክርስቲያኖቹ በላይ ሲያገለግል የነበረው፤ ተዝካራቸው መውጣት አለበት ብሎ ከካህናቱ ጋር የሚሟገተው፣ ድንበር ተሻጋሪውና ድልድይ ገንቢው መሐመድ ካሣ ለኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች ፍቅር ከበቂ በላይ ማሳያዬ ነው፡፡

ያየሁት፣ የነካሁት፣ የበለጠኝ ማስረጃዬ፤ ፈጠራ አያስፈልገኝም።

ኤፍሬም ሆይ በረከትህ ይደርብን።

 ------------------------------------------- / / / --------------------------------------------