Sunday, January 27, 2013

“ቁጣንና ሌሎችንም አስመልክቶ የቅዱስ ኤፍሬም ተግሣጽ”


      "አንተ መንፈሳዊ ተፈጥሮ" አለህ። ነፍስህም የእግዚአብሔር አርዓያና አምሳል ናት። እናም ከሰው ሁሉ ጋር በፍቅር በመኖር የእግዚአብሔር አርዓያ የሆነችውን ነፍስህን አክብራት። በምትኖርባቸው ዘመኖችህ ሁሉ በተቻለህ መጠን ሰውነትህን ከቁጣ ጠብቅ። ያለበለዚያ አንተን ወደ ሲኦል ታወርድሃለች፤ ጎዳናዎቿም ወደ ገሃነም የሚያመሩ ናቸው። እናም ቁጣን በልብህ አታኑራት መራርነትንም በነፍስህ አታሳድር በነፍሰህ ላይ አንዳች ሥልጣን የለህምና ነፍስህን መልካም በማድረግ ጠብቃት

 

አንተ በእግዚአብሔር ደም ወደ እርሱ ቀርበሃል በክርስቶስ ሕማምም ድነኀል፤ አንተ በፈንታህ ለኃጢአት ሥራዎች የሞትክ ትሆን ዘንድ ስለአንተ መተላለፍ እርሱ ሞቷል አይሁድ በመዘበት በፊቱ ላይ ምራቃቸውን ሲተፋበት መታገሡ ሰዎች ቢያፌዙብህ እንኳ እንድትታገሣቸው አርአያ ሊሆንህ ነው መራራና ሆምጣጣ የሆነውን ወይን መጎንጨቱ ከቁጣ ትሸሽ ዘንድ ነው በጅራፍ ተገርፎ በሰንሰለት ታስሮ መጎተቱ ስለጽድቅ ስትል መከራን እንዳትሰቀቅ ነው

   ስለእውነት አንተ የእርሱ አገልጋይ ባሪያው ከሆንክ ቅዱስ የሆነውን ጌታህን ፍራው ስለእውነት አንተ የእርሱ እውነተኛ ደቀመዝሙር ከሆንክ የመምህርን ፈለግ ተከተል የክርስቶስ ወዳጅ ትባል ዘንድ ባልንጀራህ በአንተ ላይ ቢሳለቅ ታገሠው ከመድኃኒዓለም የተለየህ እንዳትሆን በሰው ላይ ቁጣህን አትግለጥ

Sunday, January 20, 2013

ስለ ቅዱሳን አበው አጥንት /አፅም/ ስናወራ ይህን እናስብ!

ስለ ቅዱሳን አበው አጥንት /አፅም/ ስናወራ በሁለት መንገድ እንመልከት፦ ይኸውም አንደኛው የግያዝ ዓይኖች (በዚህ ዓይን መንፈሳዊውን ነገር ለመረዳት ስለሚከብድ ባናይበትና ባንመለከትበት እመርጣለሁ) ይህ የግያዝ ዓይን ስጋዊ ደማዊ ብቻ ነው የሚመለከተውና።

ሁለተኛው ደግሞ የኤልሳዕ ዓይኖች፥ ክርስቲያን እንደ መሆናችን መጠን በኤልሳዕ ዓይኖች ስናይ የራቀው ቀርቦ የተሰወረው ተገልጦ በእዝነ ህሊና በዓይናችን ስናይ እንደ እግዚአብሔር ፍቃድና አሳብ የተጋደሉ የቅዱ አበው አጥንት /አጽም/ መጽሐፍ ቅዱስ የሚለንን ዘጠኝ የሚያህሉ እውነታዎችን በደንብ እንረዳበታለን! ይኽውም፦

Friday, January 18, 2013

ስሞት እጸልይላችኋለሁ


                                                                           በዲ/ ሄኖክ ኃይሌ
  ከመውጣቴም በኋላ እነዚህን ነገሮች እንድታስቡ በየጊዜው ትችሉ ዘንድ እተጋለሁ!” /2 ጴጥ.113-15/

       ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም በመጣበት ወቅት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መሥርቶአል፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያቱንእኔን ማን ትሉኛላችሁ?” ብሎ በጠየቃቸው ጊዜአንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህብሎ ቅዱስ ጴጥሮስ መልሶ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላአንተ ዓለት ነህ በዚህችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራታለሁ፤ የሲኦልም ደጆች ሊያናውጿት አይችሉም፡፡በማለት ቤተ ክርስቲያንን በሐዋርያት መሠረት ላይ መሠረተ። /ማቴ.16÷16-18/

Wednesday, January 16, 2013

እጹብ ድንቅና ምርጥ የሆኑ አስራ ስድስቱ ብሒለ አበው!

 1 ‹ራስህን በሐሰት አትውቀስ ራስን መክሰስ ትህትና አይደለም ታላቁ ትህትና ሰዎች ሲወቅሱህ መታገስ ነው።›› /ቅዱስ ስራፕዮን/
2 ‹‹የማታምንበትን ነገር ለሰው ስትል አትስራው ከሰራኸው እንደምትጠፋበት እወቅ።›› /መጽሐፈ ምክር/
3 ‹‹አንደበቱን ከቧልት ከሐሜት ያየውንም ሚስጥር ከመናገር የሚከለከል ሰው ልቦናውን ከኀልዮ ኃጥያት ያርቀዋል።›› /አረጋዊ መንፈሳዊ/
4 ‹‹ ጸጋ ቢሰጥህ በተሰጠህ ጸጋ አመስግን ያልተሰጠህን እሻለሁ በማለት የተሰጠህን እንዳታጣ።›› /ማር ይስሐቅ/
5 ‹‹ራሱን የሚንቅ የሚያቃልል ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ እውቀትን ያገኛል አዋቂ ነኝ የሚል ሰው ከፈጣሪው ‹ጥበብ ይለየዋል።›› /አረጋዊ መንፈሳዊ/

Monday, January 14, 2013

ተግሳፅ፣ ምክርና ትዕዛዝ፦ (ክፍል ሦስት)

                ፈላስፋው ህርቃን፦ ያዘዘው ትዕዛዝ የመከረው ምክር ይህ ነው

ልጄ ሆይ፦ ከዐዋቂዎችና ከብልሆች ሰዎች አትራቅ፥ ምንም እንኳን ጥበባቸውን ባትየዝ ቁጥርህ ከእነርሱ ጋር ይሆናልና ሲልኩህም ሁለተኛ ጓደኛን ጨምሩልኝ በማለት አታስቸግራቸው።

ልጄ ሆይ፦ ባልንጀራህን ስትልከው እሺ በእጄ ያለህ እንደሆነ ባልንጀራው እንጂ ጌታው አለመሆንህን አስብ። ዳግመኛም የላከኸውን አቃንቶ ሲመለስ ይህን አጎደልኸ በማለት አታበሳጨው። እሱ ገንዘቡ ያልሆነውን አይበላምና ያንተም ያልሆንውን ለማምጣት አያዝንልህምና።

ልጄ ሆይ፦ ከባዕድ ሰው ማዕድ መቅረብን አትውደድ (ቀላዋጭ አትሁን) እንዲህ ያለው ነገር ያዋርድሃል ያስንቅሃልና።

“የሌላ ማዕድ ደጅ የሚጠና ተስፋ የሚያደርግ ሰው አነዋወሩ እንደ ሞተ ሰው ነው እንጂ እንደ ደኅነኛ አይደለም የሰው እህል የሚወድ ሰው ከሐሜት አይድንም የተመከረ አዋቂ ሰው ግን ከሁሉ ይጠበቃል።” /ሲራ 40፥29/

Saturday, January 12, 2013

"መንፈስ፣ አእምሮና ልሳን"


ይህቺን አነስተኛ ጽሁፍ እንድጽፍ ያነሳሳኝ ወንድም ታረቀኝ “የመንፈስ መውረድና ልሳን” በሚለ በመጣጥፉ በመነሳት ሲሆን ከአንዳንድ ወንድሞቼና እኅቶቼ ስለ አሉታዊ ግምት በመውሰድ ከመጽሐፍ ቅዱስ ቃ እየተረሙት ስለ እግዚአብሔር በፈ መጠን እነአልኩኝ።

ከአንዳንድ ወንድሞቼና እኅቶቼ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ቃል ስንንነጋገር ስለ ልሳን በ1ኛ ቆሮንቶስ በምዕራፍ 14፥2 ላይ ያልውን ሐረፈተ ነገር  በመጥቀስ እንዲህ ብለውኝ ነበር  "በልሳን የሚናገርስ ለእግዚአብሔር እንጂ ለሰው አይናገርም" እና እኛ በልሳን ብንናገር ለእግዚአብሔር፣ ከእግዚአብሔር ጋር እንጂ ለሰዎች ወይንም ከሰዎች ጋር አይደለምነበር ያሉኝ።  እኔም እነሱ ላነሱልኝ  መጽሐፍ ቅዱስ በ1ኛ ቆሮንቶስ በምዕራፍ 14፥2 ላይ ያለውን ቃል ስለጠቀሱልኝ ነገሩን በአርሞ ለትንሽ ደቂቃዎች አሰላሰልኩና ማለፍ ሳላልፈለኩኝ እንዲህ ነበር ያልኳቸው።

Tuesday, January 8, 2013

ተግሳፅ፣ ምክርና ትዕዛዝ፦ (ክፍል ሁለት)

               ፈላስፋው ህርቃን፦ ያዘዘው ትዕዛዝ የመከረው ምክር ይህ ነው
ልጄ ሆይ፦ እግዚአብሔር ባደለህና በወሰነልህ ሀብት አመስግነህ ኑር። እርሱ  እግዚአብሔር ከሰጠህ ሌላ ምን ምን የሚጨምሩልህ የለምና ተስፋህንና እምነትህን በአገልጋዮችህ ላይ አታድርግ።

ልጄ ሆይ፦ የማትወደውንና የማይወድህን ሰው ከማእድህ አታግባ። በማናኛቸውም ነገር ከማይወድህ ሰው ጋር አባሪ አትሁን። ከሁሉ ጋር መቀመጥን አትውደድ።

Monday, January 7, 2013

ተግሳፅ፣ ምክርና ትዕዛዝ፦ (ክፍል አንድ)

               ፈላስፋው ህርቃን፦ ያዘዘው ትዕዛዝ የመከረው ምክር ይህ ነው

ልጄ ሆይ፦ የምነግርህን ቃሌን ስማ ልዑል ክቡር የሚሆን እግዚአብሔርን እንድታስታውሰው ምክሬን ተቀበል።

ልጄ ሆይ፦  ነገርን (ምስጢርን) የሰማህ እንደሆነ በልብህ ውስጥ ሰውረው ለሌላ አትግለጠው። ተመልሶ የእሳት ፍም ሆኖ አንደበትህንና ኣካላትህን ሁሉ እንዳያቃጥልህ። በዚያው ላይ እገሌ ምስጢር አይቋጥርም አሰኝቶ ስድብንና ውርደትን ያስከትልብሃል።

ልጄ ሆይ፦  ዓይንህ ያየውን ሁሉ አትሳብ (አታንሣ)፣ ታስሮ ያገኘኸውን አትፍታ፣ ተፈትቶ ያገኘኸውን አትሰር፣ ተከድኖ ያገኘኸውን አትክፈት፤ ተከፍቶ የቆየህን አትክደን።

Saturday, January 5, 2013

ከንብ፣ ከውሻ፣ ከእባብ ምን እንማር?

            እውነት ነው፥ አብዛኞቻችን እነዚህ ስሞች ስንሰማ ከፊታች የሚታየንና በህሊናችን የምናስባቸው፣ የምናሰላስለው ጎጂ መሆናቸው ነው። ለመሆኑ በበጎ ጎን እይታ ስንቶቻችን ተመልክተናቸው። ማጋነን ባይሆንብኝም በተቃራኒ እይታ ነው አብዛኞቻችን የምንመለከታቸው። ለዚህም ነው ከንብ፣ ከውሻ፣ ከእባብ ምን እንማር?” ብዬ እርስ የሰጠሁት። ንብን የምናውቃት በተናዳፊነቷ ነው፣ ውሻን ደግሞ በተናካሽና በአስደንጋጭነቱ ነው፤ እንዲሁም ደግሞ እባብን መርዘኛና ገዳይ እንደሆነ ነው። እንግዲያውስ ከተለያዩ ጸሐፊያንና መምህራን ያነበብኳቸውንና የሰማሁትን እነሆ ለእናንተ ለወዳጆቼ አብረን በጎ በጎ ጎናቸውን እናነበው ዘንድ አቀረበኩ። መልካም ምንባብ!