Wednesday, September 30, 2015

በመልአከ መንክራት ግርማ ወንዱሙ ላይ ማጉረምረም ለምን? ክፍል ፪



እኔ ታናሽ ብላቴና ይህንን ጹሑፍ እንዳዘጋጅ ያነሳሳኝ ነገር ስለ  ሦስት ዓበይት ነገር ነው።

አንደኛ፦ ከአንድ ዓመት አምስት ወር በፊት የምንወድው ውዱ ወንድማችንና መምህራችን ቀሲስ ሕብረት የሺጥላ «አጋንንትን ከሰዎች የማስወጣት ሥርዓት» በሚል ባስተማረው ትምህርት በዚህ ትምህርትህ ላይ መምህራችን ስም ሳይጠቅስ (ስለ መልአከ መንክራት ግርማ ወንዱ ያስተማረው ትምህርት እንደሆነ ነው በቀጥታ የተመለከትኩት።)

ኹለተኛ፦ በፕሮቴስታንታዊ ተሀድሶ የሚመራው መለከት የተባለ ሬድዮ ያሰራጨው የሐሰት ዶሴና ክስ፤ ጲላጦስና ሄሮድስ የማይስማሙ ኾነው ሳለ ክርስቶስን አሳልፈው ለመሰጣጠት ለጊዜያዊ ጥቅማቸው ሲሉ አንድነታቸውን አበረቱ፤ እንዲሁም ደግሞ መልአከ መንክራት ግርማ ወንዱሙ ለማሳደድ አንዳንድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ጉያ ከተሰገሰጉ ፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ጋር በማበር ለጊዜያዊ ጥቅማቸው ሲሉ አንድነታቸውን አበረቱ፤ ሲያብሩ አየን፤ ሰማን።

እነዚህ አንዳንድ ዘለባብዳን /ዘለባጆች "መለከት ሬድዮ" በተባለ በድምፅ ማሠራጫ ባስተላለፉት የድምፅ ማዕደር የወንጌል ሥራ ከእኛ ጋር የሚሰሩ የተባሉ፤ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ጉያ ከተሰገሰጉ ፕሮቴስታንት ተሐድሶ ከኾኑት ከእነ አቶ ጽጌ ስጦታው፣ ከእነ አቶ ሙሴ መንበሩ ጋር (እነዚህ በይፋ የተወገዙና የተለዩ ቢኾኑም ሌሎች ያልተወገዙና ያልተለዩ አሉ) መረቡን የዘረጋው ፕሮቴስታንታዊው ተሀድሶ ቡድን ነው፤ ይሄ ቡድን የተለመደውን መዘለባበጃቸውን ለይስሙላ በመልአከ መንክራት ግርማ ወንዱሙን በማነጣጠር፣ የመምህር ግርማ ወንዱሙን መንፈሳዊ አገልግሎታቸውንም እንነቅፋለን ቢሉም ቅሉ ግን አጠቃላይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ዶግማንና ቀኖናን ያነጣጠረ ነበር። ይሄም፥ የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ አባቶችን፣ ቅዱሳት መላእክትን፣ ጻድቃንን፣ ቅድስት ድንግል ማርያምን በማንቋሸሽና በማጥልሸት፤ የተለመደው የኑፋቄ መርዛቸውን ሲረጩ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው።

ጠቢቡ ሠለሞን በምሳሌው፦ "በቃል ብዛት ውስጥ ኃጢአት ሳይኖር አይቀርም፤ ከንፈሩን የሚገታ ግን አስተዋይ ነው።" /ምሳ 1019/ ብሎ እንዳዘዘን፤ እኛም ከንፈራችን የተባለው፥ አንደበታችን ሰብስበን፤ ይሄንን የድምፅ ማዕደርን በመስማት እውነቱን እንወቅ!።