Saturday, November 30, 2013

ፕሮቴስታንቶች (ተሐድሶ) የተሟላ መጽሐፍ ቅዱስን አይቀበሉ፦



ፕሮቴስታንቶች (ተሐድሶ) በሐዲስ ኪዳን ውስጥ በማስረጃነት ደረጃ የተጠቀሰ ጥቅስ የለም ይላሉ። ይህ አባባላቸው የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን በደንብ ካለማንበባቸው የተነሣ እንጂ በብዙ ቦታዎች እንደተጠቀሱ ማስረጃዎችን ከብሉይ ኪዳንም ከሐዲስ ኪዳንም እንደሚከተለው መጥቀስ ይቻላል!

ፕሮቴስታንቶች (ተሐድሶ)፦ ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የሚፈልጓቸውን ብቻ በመውሰድ ሌሎችን ትተዋቸዋል። በመሆኑም እነርሱ በሚቀበሏቸው እና ቤተ-ክርስቲያናችን በምትቀበላቸው መጻሕፍት ቁጥር መካክል ልዩነት አለ።

1.        የፕሮቴስታንቲዝም መስራች ማርቲን ሉተር ለእርሱ ትምህርት የማይመቹ የመሰሉትን መጻሕፍት እያወጣ ይጥል ነበር። ለምሳሌ፦ የያዕቆብ መልእክት ስለ ምግባር አስፈላጊነት ሰለሚያስተምርና ይህም ማርቲን ሉተር ስለ ጸጋ እና እምነት በቻ ይሰብከው ከነበረው ትምህርቱ ጋር አልሄድ ስላለው መልእክቱን ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አውጥቶት ነበር። እንዲያውም “Epistle of straw ገለባ መልእክት” ብሎ እስከ መጥራት ደርሶ ነበር።

2.      አንዳንድ ወገኖች ከ66ቱ መጻሕፍት ውጭ ያሉትን መጻሕፍት “አፖክሪፓ” ብለው ይጠሯቸዋል። ይህ ግን የተሳሳተ ስያሜ ነው። “አፖክሪፓ” በጥንት ዘመን ምሥጢራዊ ለሆኑት የጥንቆላ መጻሕፍት የሚሰጥ ስም ነውና። እኛ ግን፥ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍቱን፦ “ሁለተኛ የቀኖና መጻሕፍት - ዲዮካትሮኒካል” እንላቸዋለን።

3.      የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ሁለት ዓይነት የኖና ክፍሎች አሏቸው። እነርሱም፦ የመጀመርያ-ፕሮቶካኖኒካል፣ እና ሁለተኛ- ዲዮካትሮኒካል ይባላሉ።

Tuesday, November 26, 2013

ከቤተ-ክርስቲያን የተገኙ ልጆቿ፦


ከጻድቁ ኢዮብ ትምህርትና ምክር የተነሳ፥ በዙሪያው የነበሩትን የነነዌ መርከበኞችን፣ ነጋዴዎችን፣ መኳንቶችን፣ ከደቂቅ እስከ አዋቂ፣ አጠቃላይ በወቅቱ የነበሩትን ስለሁናቴው ሲገልጽል "ሰዎች፥ እኔን ሰምተው በትዕግሥት ተጠባበቁ፥ ምክሬንም ለማዳመጥ ዝም አሉ።" ብሎ ተናግሯል። ነቢየ ዕንባቆም "እግዚአብሔር ግን በተቀደሰ መቅደሱ አለ ምድርም ሁሉ በፊቱ ዝም ትበል።" /ዕን 220/ ብሏል። በማቴዎስ ወንጌልም፥ ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ ሰለ አምላካችንና ስለ መድኃኒታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ የባህሪው አምላክነቱንና ሲያመለክት፤ "ኢየሱስም፦ ዝም በል ከእርሱም ውጣ ብሎ ገሠጸው።" /125/ ይላል፤ እዚህ ጋር እርኩሳንነን አጋንትን በቃሉ የሚያዝ ስለሆነ "ዝም በል ከእርሱም ውጣ" ብሎ ገሠጸው እንጂ "አባት ሆይ፥ በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ" /ዮሐ 1723/ ይህንን አጋንት፥ አሶጣልኝ፣ ላሶጣ፣ ወይንም እናውጣ፤ ብሎ አልጻፈልንም፣ አልሰበከንምም። የሆነው ሆኖ ግን ይህንንም ሥልጣነ ፈውስ (አጋንትን መገሠጽ) ራሱ ባለቤቱ የሰጣቸው ጸጋ ነው።

እንግዲህ የእግዚአብሔር ልጆች በተቀደሰ መቅደሱ ቤተ-ክርስቲያን ያሳደገቻቸው ልጆቿ፥ ሲናገሩ፣ ሲያስተም፣ ሲዘምሩ፤ የእግዚአብሔርን ቃል ከአንደበታቸው ሰምተው በትዕግሥት ይጠባበቃሉ፣ ምክሩም፥ ግሩምና ድንቅ ከመሆኑ ብዛት የተነሳ ለማዳመጥ ዝም ይላሉ! ምድሪቱንም በቃላቸው ይገስጿታል፥ ከመገሰጿም የተነሳ በፊታቸው ዝም ትላለች። እንዲሁም ከራሱ ከባለቤቱ የተቀበሉት ጸጋ ነውና፥ እነ ቅዱስ ጳውሎስ አጋንትን ሲገሥጹ እንደነበር በዘመነ ሐዲስ ተመዝግቦልናል። በዘመናችንም የተባረኩና የጸጋ ተካፋይ በሆኑት አባቶች ሥልጣነ ፈውስ (አጋንትን እየሠጹ) ዝም ሲያስብሉና ሲያሶጡ እያየን ነው፥ ደግሞም የእግዚአብሔ እጅ መች ይታጠፍና፤ ገና እናያለን።
 
 
እነዚህ ሁሉ፥ ከአንዲት፣ ከቤተ-ክርስቲያን የተገኙ ልጆቿ ናቸው፣ አምላካቸውና መድኃኒታቸው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ብዙ ሞግዚቶችና አእላፍት አሏቸው!





Sunday, November 24, 2013

ስለ ጾም ጠቃሚ ምክር፦



1. ጾም ማለት ከእግዚአብሔር የታዘዘ እውነተኛ ሕግ ነው። ነገር ግን የሥራውን ፍሬ መጀመሪያ እንገልጻለን፤ ጾም ማለት መጀመሪያ ዓይናችን ክፉ ነገርን እንዳያይ፤ ጆሮአችን ክፉ ነገርን እንዳይሰማ፤ አንደበታችን ክፉ እንዳይናገር መከልከል ነው እንጂ እንዲያው ሥጋና ቅቤን ብቻ መተው አይደለም።

መቼም የሰው ባሕርይ በዚህ ዓለም ሲኖር ሁል ጊዜ በደስታና በተድላ ለመኖር ነው የሚጥረው፤ ይኸውም ለሰው ልጅ ሐሳብ ሁለት መንገድ አለው፤ አንዱ በሕግ የተፈቀደ፤ ሁለተኛው በሕግ ያልተፈቀደ ነው። በሕግ ያልተፈቀደ ማለት እግዚአብሔርንና ሰውን የሚበድልበት የዓመጽና የኃጢአት ጎዳና ነው።

 አባታችን አዳም ከሕግ የወጣ መንገድ ያልታዘዘውን ሥራ ሠርቶ በልቶ ከገነት ወጥቶ ወደ ግዞት እንደሄደ ያመለክተናል። በሕግ የታዘዘ መንገድ ማለት ሰው በዚህ ዓለም ሲኖር ሀብታምም ቢሆን ወይም ድሃ፤ ያንኑ የመጀመሪያ ዕድሉ የሰጠውን ሀብት በምስጋና ተቀብሎ ፈጣሪውን እያመሰገነ በጾምና በጸሎት፤ ወይም በሐዘንና በደስታም ቢሆን እግዚአብሔርንና ወንድሙን ባይበድልና ሳያስቀይም ‹‹ላብህን ከግንባርህ ጠርገህ እንጀራህን ብላ›› /ዘፍ3፡19/ እንደተባለው ሕግን ቢፈጽም፤ እስከ ዘለዓለም የሕይወቱ ምንጭ ሳይደፈን ይኖራል።

የጥፋት ልጆች ዛሬ ግን ሰዎች ጾምና ጸሎትን እግዚአብሔር የማይፈቅደው ሕግ ነው፤ እግዚአብሔር የሚወደውና የታዘዘው ሕግ ያገኙትን ሁሉ ሳይጸየፉ መብላትና በደስታ መኖር ነው፤ ብለው በሆቴል ሜዳ ያገኙትን እንደ ጨፌ ሣር የለመለመ መብልና መጠጥ እየተመገቡ እናያለን። ነገር ገን ይህ እግዚአብሔር የሚወደው ሕግ ይሆን? በእውነት እግዚአብሔር የሚወደው ሰው አጭር ጊዜ በሆነ ሕይወቱ በዚህ ዓለም ላይ ሲኖር ለእርሱ ሲል የተሰቀለለትንና የሞተለትን ፈጣሪው ሁል ጊዜ እያሰበ በጾምና በጸሎት በሐዘንና በትዕግሥተ ሆኖ ወደ ፈጣሪው ዓይነ ሕሊናውን ሰቅሎ፤ ዘለዓለማዊ የሆነውን ብርሃናዊ ሕይወት ተጎናጽፎ መኖር ነው። በዚህ ዓለም ተድላና ሕይወት ለእኛ ነውና የተፈጠረው ብለው ሲፈነጥዙ፤ ቢኖሩ፣ ‹‹ሞት ሲመጣ ጥሩ ቄስ፤ ጦር ሲመጣ ግዙ ፈረስ›› የተባለው ተረት በእነርሱ ላይ ይፈጸማል

Tuesday, November 19, 2013

የተቃውሞ ሰልፍ በሮም ከተማ



       



       የተቃውሞ ሰልፍ በሮም ከተማ የሳዑዲ አረቢያ ኤንባሲ፤ በመሄድ የተቃውሟችን ድምፃችንን ለማሰማት፥ በሰልፍ ላይ ትውለደ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊን፣ ሃገር ቢለየንም ደማችን አንድ ነው ብለው ትውልደ ኤርትራውያንና ኤርትራዊያን፣ እንዲሁም በሰልፍ ላይ የተካፈሉ በርከት ያሉ የኢትዮጵያዊያን ወዳጆች ጣልያዊያን፤ አብረን ነበርን። ለሦስት ሰዓታት ያህል፥ በሳዑዲ ሃገር፦ በዜጎቻችን ላይ የሳዑዲ ሕዝብና መንግስት የሚደርሱባቸውን ጥቃት፣ እንግልት፣ ድብደባ፣ ግድያ፤ በጥብቅ ተቃውመን፤ ለዓለሙ ሕዝብ በአጽኖት እንዲመለከተውና እንዲከታተለው እኛ ኢትዮጵያዊያንና የኢትዮጵያን ወዳጆች በሙሉ፤ ተቃውሟችንን በጋለ ሃገራዊ የፍቅር ስሜት፣ በሠላማዊ መንገድ፤ በሚገርምና በሚያስደንቅ ሁኔታ አሰምተናል።

ይህንን ሃገራዊና የማንንታችንን ጥያቄ በመጠየቅ፥ ላስተባበሩና በተቃውሞ ሰልፍ ላይ የታደሙትን፣ እንዲሁም የሮም ከተማ አስተዳደርን እጅግ ከፍ አድርጌ ከልብ አመሰግናቸዋለሁ።

Saturday, November 16, 2013

ሰበር ዜና፦ የመጨረሻው መጀመርያ



ሳውዲ ከሪስ አብደላ ሚባል አካባቢ ዝናብ በአሁን ሰዓ መብራት ፍቶ ከተማው ጎረፍ ላይ ነው በአረባ አመት ውስጥ ታይቶ ማይታወቅ ይለኛ ዝናብና ጎርፍ አስተናግዳለች ሳውዲ ሆይ የማይነኩትን የቅድስት አገር ኢትዮጵያ ልጆች ነክተሻልና ፍርድሽን ከላይ ተቀበይ! (ፍሪደም ፎር ኢትዮጵያ)


የመጨረሻው መጀመርያ፦

የመጨረሻው መጀመርያ፥ ማለቴ፦ ለእነርሱ የመጨረሻ፣ ለፈጣሪያችን ደግሞ ሥራውን የሚጀምርበት መጀመርያ፤ ማለቴ ነው!!!

እግዚአብሔር፥ በነቢዩ ኢሳያስ አንደበት አድሮ፤ ሕዝብን ለሚጨፈልቁ፣ ክቡር የሆነውን የሰውን ደም እንደ ውሃ ጅረት በእጃቸው ላጨማለቁ፣ እንደዚህ ይላል፦ "በዚያም ቀን የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ወደ ልቅሶና ወደ ዋይታ ራስን ወደ መንጨትና ማቅንም ወደ መልበስ ጠራ።" እውነት ነው! በየትኛውም ዘመን ይሁን - በየትኛው ጊዜ፤ አምላክ ብድራታቸውን ጠርቶ ይመልስባቸዋል።

በመቀጥል፥ ለተበደሉ፣ ላዘኑ፣ ለተጨነቁ፤ ሕዝብ ደግሞ፦ "እኔም በኢየሩሳሌም ሐሤት አደርጋለሁ በሕዝቤም ደስ ይለኛል ከዚያም ወዲያ የልቅሶ ድምፅና የዋይታ ድምፅ አይሰማባትም።" /ኢሳ 2212 እና 6519/ ብሎ ተናግሯል!

ኧረ ለመሆኑ፥ ደስታና ሐሤት የሚያደርግባቸው፣ ሕዝቦች የተባሉት እነማን ይሆኑ? ሕዝብን እየጨፈልቁ፣ ክቡር የሆነውን የሰውን ደም እንደ ውሃ ጅረት በእጃቸው እያጨማለቁ፣ እያረዱና እየገደሉ፤ "ይቅርታ" ጠይቁኝ በሚሉት ይሆን ሐሤት የሚያደርገው? እንደ መለኮታዊ ቃሉ ግን፥ በኢየሩሳሌም አምሳል የተጥራችው ሃገረ ኢትዮጵያና ፈሪሐ እግዚአብሔር ባደረባቸው ሕዝቦች ደስታና ሐሤት ያደርግባቸዋል።

ለምን ቢሉ እንደ ሰማእቱ እስጢፋኖስ፥ እያዘኑ፣ እየተጨነቁ፣ እየተበደሉ፣ እየታረዱና እየተገደሉ፤ ሰይፍና ጎመድ ይዘው አልዝመቱምና። እንደውም አብዝተ እንደ መዝሙረኛው ንጉሡ ዳዊት "ጠላቶቼ ሁልጊዜ ይሰድቡኛል፥ የሚያሳድዱኝም ተማማሉብኝ። አመድን እንደ እህል ቅሜአለሁና፥ መጠጤንም ከእንባዬ ጋር ቀላቅያለሁና" /መዝ 1028-9/ በማለት የዘመረውን ዝማሬ አብዝተው ዘመሩ እንጂ!!!

ታዲያ ንጉሣችንና አምላካችን ይታደገናል! ስለዚህ ደስታና ሐሤት የሚያደርግባቸው ሕዝቦች ስለሆንን ክብር ይመስግንልን  ለምላካችን!!!
 
                    ዋቢ፦
 
       2  አረብ ኒውስ

Saturday, November 9, 2013

የመድኀነ-ዓለም ወዳጅ ሆይ፦


የመድኅነ-ዓለም ወዳጅ ሆይ፦ አንተ የኢየሱስ ክርሰቶስ ወንጌል አምናለሁ ብለህ፥ የማዳኑን፣ የቤዛነቱን፣ የቸርነቱን፣ የምህረቱን፣ እንዲሁም የሁሉ ነገር ማሰሪያና መቋጫ የሆነውን የፍቅሩን ብዛት ቀመሰህ፤ ቃሉን ስትሰማ፣ ወንጌሉን ስታነበው፣ ልብህ በሐሴት እንደሚረካ አልጠራጠርም።

የመድኅነ-ዓለም ወዳጅ ሆይ፦ ታዲያ ልብህ በቃሉ የሚረሰርስና የሚረካ ከሆነ፥ ለአገልግሎት ስትዘጋጅ፤ ማለትም፦ ለማሰተማር፣ ለመስበክ፣ ለሕዝበ-ክርስቲያኑ ሆነ ለዓለም በሥነ-ጹሑፍ ስትገልጠው፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለም ካዳነበት ምስጢረ ሥጋዌ እያነፃፀርኸ፥ ነቢያቱን፣ ሐዋርያቱን፣ ሰማእታቱን፣ ቅዱሳን መልአክቱንና የጌታ እናቱን ቅድስት ድንግል ማርያምን፤ ተገቢውን ቦታ አለመስጠት፥ ለማሳነስ መሞከር፤ አትሞክር። ምክንያቱም በእርሱ ዘንድ ሁሉ እንደተፈጸመ እወቅ።

ምኑ እንደተፈጸመ ትል ይሆናል። ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን መድኃኒዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ለወዳጆቹ ለቅዱሳኑ የእርሱ የነበረውን፥ ሥልጣን፣ ኃይልን፣ የተለያዩ የመንፈስ ቅዱስ የፀጋ ስጦታዎች እንደሰጣቸው ልብ ይመን። እንግዲህ እነርሱ ከባለቤቱ የተቀበሉት ስጦታ ስለሆነ፤ ክብር ለሚገባው፥ ክበር መስጠት ተገቢ ነውና ነው።

የመድኅነ-ዓለም ወዳጅ ሆይ፦ ፍጹም የሆነ፥ የመንፈስ ቅዱስ የፀጋ ስጦታዎች ስለሆነ ነው። እነዚህ የፀጋ ስጦታዎች የተለያዩ ቢሆኑም፥ የማዳን፣ የመገሰፅ፣ የመፈወስ፣ የማስተማር፣ የመተርጎም፣ የመዘመር፣ የማመስገንና የተመስጦ፤ እርሱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አንዴ ባርኮና አበዘቶ ስለሰጣቸው እንደሆነ ሁሌም ቢሆን ከሕሊናህ፣ ከልቦናህ፣ ከአእምሮህ፣ ከሃይማኖትህና ከእምነትህ ቃል አንፃር እየው።


Thursday, November 7, 2013

ኧረ ሃገር አለኝ!



ሃገር አለኝ፥ ኧረ ሃገር አለኝ!
ያውም ቅኝ ግዛት ያልገዛኝ፣
በጀግኖቿ ልጆች ደም ታሪክ  ያለኝ፣
የፍቅር ሃገር አብሲኒያዊነኝ።

ከያኔዎች መሪዎች ወኔና ጥንካሬያቸው፤
እስኪ አንዱን አጼ አይለስላሴን እናውሳቸው

ጀርመኖች በሁለተኛ ዓለም ጦርነት ሳለች፣
ወደ ኢትዮጵያ ንጉስ መልዕክት ላከች፣
ለሥራችን የሚሆን ሰራተኛ ስጡኝ አለች፣
አይሆንም ብላ ኢትዮጵያም መለሰች።

በሠራተኛ ሒሳብ ይወስዱና፣
ላልተገባ ሥራ ያቆሙና፣
ቁረጥ ፍለጥ ያስብሉና፣
እኛንም ያስቆጥሩን ነበርና።