Saturday, August 24, 2013

“አዳም የት ነህ?” በቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)


ከሩቅ ይሰማኛል
የቤተ- ክርስቲያን ደውል

ነፍስን የሚያማልል
ልብን የሚያባብል

እንደ አዲስ የሆነ
እንደ አዋጅ የሆነ
ከቀኑ ሁሉ ጠዋት እሁድ የገነነ
ከእለት ሁሉ ግህዝ እሁድ የገነነ

ማለዳ ሰንጥቆ የሚያስገመግም
ሠመመን መሳይ ድምፅ ከሩቅ ሚሰማ
ቀላቀሎ የያዘ የካህናት ወረብ የካህናት ዜማ

ንፋስ የሚያመጣው አልፎ-አልፎ ሽው የሚል
ተነስ ቀድሰ የሚል አዳም የት ነህ የሚል

Tuesday, August 6, 2013

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም (ክፍል ሁለት)

በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ


ቤተክርስቲያን እመቤታችንን የምታከብርበት አስፈላጊና ዋና ዋና ምክንያቶች

1.        መንፈስ ቅዱስ ስለጸለላት /መንፈስ ቅዱስ በርሷ ላይ ስለሆነ/፣
2.      የእግዚአብሔር እናት /እመአምላክ ስለሆነች/፣
3.      ዘለማዊ ድንግል ስለሆነች፣
4.      ቅድስት ስለሆነች፣
5.      መንፈስ ቅዱስ ስለመሰከረላት፣
6.     ጌታ ራሱ ስላከበራት፤
7.      ስለ ተአምራቷና ስለተቀደሰው መታየቷ ናቸው። ይህም /በተለያየ ጊዜያት/ በግብጽ የመገለጽ ክብር ነው።

ክብሯም፦ በቤተክርስቲያን ንዋየቅዱሳት፣ በመዝሙራት፤ በቤተክርስቲያን ጸሎት ምልጃዋን በመለመን በዓላቷን በማክበር እና አንዱን ጾማችን በስሟ በመጾማችን ይገለጣል።