ደራሲ ዶ/ር እጓለ ገብረ ዩሐንስ ከጻፉት መፅሐፍ ስለ “ሞራል ድቀት” ብፁዓን ንጹሐነ ልበ ስለ ክርስቲያን ምግባር መሠረት በሚል ለንባብ ካበቁት የተወሰደ።

እንዲህ ያለ ሰውነት ሲታገል ይቆይና ሲሰለቸው፦ የቸልተኘነት፣ የግዴለሽነት ኢንዲፈረንቲዝም መንፈስ ይሰፍንበታል። ይህ በተለይ የሚገለጸው በሥነ ምግባር መስክ ነው። ሥለታም የነበረው ሥነ ምግባራዊ በሕሊናው ይሰንፋል። የሚመቹ፣ የማይቆረቁሩ፣ የማይጋጩ እንደ ዘዴኝነት፣ ጮሌነት፣ ብልሃተኝነት፤ ያሉ የማይጨበጡ የቀልጣፋ ሰውነት ጠባዮች ያይላል። “አስመሳይ፣ አድር ባይ፣ እንደ እምነቱ የማያምን፣ እንደ ኑሮው የማይኖር፣ የሕሊናውን ብኵርና ለምስር ንፍሮ የለወጠ” ሌላም ሌላም። እንደ አለንጋ የሚጋረፉ ተግሣጾች ወቅታዊነታቸውን የሚያገኙት በዚህ ሳቢያ ይመስለናል። “የሞራል ድቀት” የሚባለው ይህ ሳይሆን ይቀራል? የመነሳቱ፣ የመቆሙ፣ ከራሱ ጋር ተስማምቶ ሚዛን ጠበቆ የመራከመዱ፤ ነገርስ እንዴት ይሆን? ቅን ሕሊና የማያልፈው ጥያቄ ነው።
+++++++++++++++++ +++++++++++++++++