Tuesday, December 25, 2012

"ስምዖንም ባረካቸው እናቱን ማርያምንም።" /ሉቃ 2፥ 34/




         *ቅድስት ድንግል ማርያምን መባረክ እነሆም፥ በኢየሩሳሌም ስምዖን የሚባል ሰው ነበረ፥ ይህም ሰው የእስራኤልን መጽናናት ይጠባበቅ ነበር፤ ጻድቅና ትጉህም ነበረ፥ መንፈስ ቅዱስም በእርሱ ላይ ነበረ። በጌታም የተቀባውን ሳያይ ሞትን እንዳያይ በመንፈስ ቅዱስ ተረድቶ ነበር። /ሉቃ 225-26/ 

ታዲያ አኚህ አረጋዊ ስምዖን በጌታ ዘንድ የተቀባውንና ለዓለም ሁሉ ቤዛ የሚሆነው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ሳያዩ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ይጠባበቁ ነበር የዓለም ቤዛ የሆነው ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሾማቸውና የቀባቸውን በዘመናችን በዓይናችን፣ እያየን በጆሮዎቻችን እየሰማን፤ እኔ ከእነሱ እኩል ነኝ በሚልና ከቅድስት ድንግል ማርያምም በምን አንሳለሁ አስተሳሰብ እየወደቁ ነውና ከእኚሁ አረጋዊ ስምዖን ጻድቅና ትጉህ ምን ይማሩ ይሆን ? ለዓለም ሁሉ ቤዛ የሆነው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሥጋዋ ሥጋ፣ ከነፍሷ ነፍስ፤ የተዋህደባት ቅድስት ድንግል ማርያምን እንዴት የውጣ ቃል ሊናገሩ ይደፍራሉ? በእርግጥ ጻድቅና ትጉህ የሆነ፣ መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ከሆነ ቅድስት ድንግል ማርያምን ይባርካል እንጂ! የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ማዳኑን ቀምሼ አይቻለሁ የሚል ከሆነ ድንግልን እንደ አረጋዊ ስምዖን ለመባረክ በመንፈስ ቅዱስ መባረክ ግድ ይላል።

        አረጋዊ ስምዖን ጻድቅና ትጉህ መሆናቸው እየተመሰከረላቸው በትህተና ሁነው እንደጠበቁ ሁሉ፤ ምናለ በትህትና ተኹኖ ድንግልን መባርክ አይሻልምን? ይህ እኔ በምን አንሳለው ባይነትና መጽሐፍ ቅዱስም ለእንደነዚህ ዓይነት ሰዎች ሥፍራም ቦታም እንደሌለው እየታወቀ። ታዲያ እንደ አረጋዊ ስምዖን ቅድስት ድንግል ማርያምን እንባርክ እነሆምስምዖንም ባረካቸው እናቱን ማርያምንም። /ሉቃ 2 34/ እነሆ፥ የብዙዎች ልብ አሳብ ይገለጥ ዘንድ፥ ይህ በእስራኤል ላሉት ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ለሚቃወሙትም ምልክት ተሾሞአል፥ በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል አላት።ድንግልን የባረከ ጻድቅና ትጉህ የሆኑ አረጋዊ ስምዖን እንዲህ ካሉ እኛማ እንዴት አናከብራት! አልቀን፣ አክበረን አንባርካታለን !!! “በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል ይሄ የሰይፍ ስለት ቶሎ አይወጣም፣ አይመዘዝ፤ ምክንያቱም ሰይፍ የሚያነሱ በሰይፍ የጠፋሉና።

       ድፍረት አይሁንብኝና አባቴ፥ጻድቅና ትጉህ የሆኑ አረጋዊ ስምዖን ልጠይቆ፦ ድንግልን ሲባርኩበአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል ያሏት እንዴት ቢሆን ነውን? ኢየሱስ ክርስቶስን በመውለዷ ነውን? አዎከአፉም በሁለት ወገን የተሳለ ስለታም ሰይፍ ”/ራአ116/ የተባለውን የሰው ልጅን ስለወለደችው።

          አባቴ፦ የቅዱሳን አምላክ፥የአብርሃም፣ የይስሐቅ፣ የያዕቆብ እንዲሁም የእርሶ ቅዱስ መንፈስ በእኔ በልጆ ላይ እንዲያድር እግዚአብሔር አምላክ ለምኑልኝ አሜን!!!

                              * ቅድስት ድንግል ማርያምና አገልገሎቷ
 
       በወንጌል ኢየሱስ ክርስቶስ ምንድን ነው ያስተማረን የሰበከንእኔ የዓለም ብርሃን ነኝይልና ሐዋርያቱ "እናንተ የዓለም ብርሃን ናቹይላቸዋል። ቅዱስ ጳውሎስም፦እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉብሏልና። /1 ቆሮ 111/ ቅዱስ ጳውሎስ ክርስቶስን መምሰሉ በአገለገሎቱ ነው፣ እናቱ ድንግል ማርያምማ እንዴት ምን ልንላት ይሆን? አገልገሎቷን ብንመለከት፣ ፍቅሯ ብናይ፣ ትህትና ብናስተውለ፣ መታዘዝዋ እጹበ ድንቅ የሆነ፣ ጌታችን ወደ ግብጽ ይዛው መሄዷ፣ በበርሃ መራቧ መጠማቷ፣ የአይሁድ ረበናት ፊትና ግልመጫና፣ የሰዱቃዊያንና የፈሪሳዊያን የቃላት ውርጅብኝ መቻሏ፣ ክርሰቶስን በመከተል ከሆነ እስከ ቀራንዮ፣ መሪር ዕንባ ስለ ልጇ እንዳነባች፤ እኛም አባቶቻችን ያዮትና የሰሙትን በጹሑፍ ተጽፎ ያስተላለፉልን ይህንመጽሐፍ ቅዱስበመንፈስ ሆነን ስናነበው ማናችን ይሆን ልባችን የማይነካው? ማናችን ይሆን ስለ እናትነቷ ብቻ ሳይሆን ስለ አገልገሎቷን ጽናት እንዴት አንናፍቅ? እረ ስንቱን ልበል ወዳጄ። በአጠቃላይ እንደ እግዚአበሔር ቃል መንፈሳዊ አገልግሎት ከዚህ የሚበልጥ የለም። ስለዚህ በአገልገሎቷን ብቻ ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው ድንግል ማርያም ክርስቶስን መሰለዋለች፣ ጌታችን ክርስቶስ እናንተ የዓለም ብርሃን ናቹ እንዳለው እመቤታችንም በአገልገሎቷን ብቻ የዓለም ብርሃናዊት ናት፣ ቅዱስ ጳውሎስ የተመረጠ ዕቃ እንደተባለው ድንግል ማርያም የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምርጥና የተመረጠች ቅድስት ዕቃ ናት፤ ታዲያ ይሄ በበአገልገሎቷን ብቻ ነው።

                * ቅድስት ድንግል ማርያም የኢየሱስ ክርስቶስ እናት
 
እናማ በእናትነቷኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ነው፣ እናቱ ናትና የአምላክ እናት ትባላለች።” “ኢየሱስ ክርስቶስ ፈጣሪ ነው፣ እናቱ ናትና የፈጣሪ እናት ትባላለች።

No comments:

Post a Comment