Wednesday, February 6, 2013

ክርስቶስ ለእኛ ኦርቶዶክሳዊያን ማን ነው?



እርሱ የእግዚአብሔር በግ ነው፤ እርሱም መሥዋዕት ነው።

እርሱ ስለብዙዎች ኃጢአት የተሠዋው ፍሪዳ ነው፤ እርሱ መሥዋዕቱን የሚያቀርብ ሊቀ ካህናት ነው፤መሥዋት ተቀባዩም እርሱ ነው።

ስለእኛ መከራን የተቀበለው እርሱ ነው፤ ስለእኛም የራራልን እርሱ ነው።

እርሱ ሙሽራ ነው፤ እርሱ ራሱ ሙሽሪትም ነው። (ከእናታችን የነሣው ሥጋ ለጌታችን እንደሙሽሪት ነው። ይህ ሥጋ ግን አምላክ በመሆኑ ሙሽራ ሆነ፤ በሐዋርያትም እኛ ለእርሱ ታጨን። ስለዚህም እርሱ ሙሽራ ነው፤ እርሱ ራሱ ሙሽሪት ነው አልን)

እርሱ  የሰርጉ ቤት ነው፤ እርሱ ራሱ  የሰርግ ቤቱ አሳላፊ ነው።

 እርሱ ገነት ነው፤ እርሱ ራሱ የሕይወት ዛፍ ነው።

እርሱ  ሰማያዊቱ ኢየሩሳሌም ነው፤ እርሱ ራሱ መቅደሳችንና ቅድስተ ቅዱሳናችን ነው።

በውኆች የተመሰለው እርሱ ነው፤ እርሱ ራሱ እኛ የምንኖርበት ዓለማችን ነው።

እርሱ  ምግባችን ነው፤ እርሱ ራሱ ስለድኅነታችን የሚመግበን መጋቢያችን ነው።

እርሱ ሕያው የሆነው ሕብስት ነው፤ እርሱ የሕይወት ውኃችን ነው።

እርሱ እውነተኛው የወይን ግንድ ነው፤ እርሱ ራሱ የደስታ ወይናችን ነው።

እርሱ ዕንቁዋችን ነው፤ እርሱ ራሱ መዛግብታችን ነው።

እርሱ መረባችን ነው፤ እርሱ ራሱ ተዋጊያችን ነው።

እርሱ የጦር መሣሪያችን ነው፤ እርሱ ሁሉን ድል የሚነሣ ነው።

እርሱ ግዝረታችን ነው፤ እርሱ ራሱ ሰንበታችንና ሕጋችን ነው።

እርሱ የቅዱሳን ኅብረት ለሆነችው ቤተክርስቲያን ራስ ነው፤ እርሱ መልካሙ የስንዴ ቅንጣት ነው።

እርሱ የወይን እርሻችን ነው፤ የእርሻውም ባለቤት እርሱ ነው።

እርሱ ግርማችን ነው፤ እርሱ እምነታችን ነው።

እርሱ ሰርጋችን ነው፤ እርሱ የሰርግ ልብሳችን ነው።

እርሱ የሕይወት መንገዳችን ነው፤ እርሱ በራችን ነው።

እርሱ የጽድቅ ፀሐያችን ነው፤ እርሱ የነፍሳችን ብርሃን ነው።

እርሱ ሕይወት ነው፤ እርሱ መንግሥተ ሰማያት ነው።

እርሱ መጀመሪያ የሌለው መጀመሪያ፣ መጨረሻ የሌለው መጨረሻ፣ አልፋና ኦሜጋ ነው።

ስለዚህም እኛ ኦርቶዶክሳዊያን በክርስቶስ ከክርስቶስ ለክርስቶስ የሆንን የክርስቶስ ነን!!!
               --------------------------------------------------------

 ዋቢ፦ ከዲያቆ ሽመልስ መርጊያ ድረ ገጽ - 12/05/2004

No comments:

Post a Comment