Saturday, June 21, 2014

"መንፈሳዊ አገልግሎት" በዲ/ን ዳንኤል ክብረት

"የእግዚአብሔርን ሥራ በቸልታ የሚያደግ ርጉም ይሁን" (ኤር ፵፰፥፲)

"እንዲሁ እናንተ ደግሞ የታዘዛችሁትን ሁሉ ባደረጋችሁ ጊዜ፤ የማንጠቅም ባሪያዎች ነን፥ ልናደርገው የሚገባንን አድርገናል በሉ።" (ሉቃ ፲፯፥፲)

አንድን አገልግሎት "መንፈሳዊ አገልግሎት" ነው የሚያሰኙት፤ እነዚህ አራት ነገሮች ሲኖሩት ነው

፩፤ አገልግሎቱ፦ ሠማያዊ ዋጋ፥ ታስቦ የሚደረግ ከኾነ ነው። የሚመራውም በመንፈስ፣ የሚሠራውም በመንፈስ ከኾነ ነው "መንፈሳዊ አገልግሎት" የሚባለው። ምድራዊ ዋጋ ታስቦ የሚደረግ ከኾነ "መንፈሳዊ አገልግሎት" አይደለም፤ ይኼ ሥራ ነው።

፪፤ አገልግሎቱ፦ በመንፈስ የሚደረግ ከኾነ ነው። የሚመራውም በሥጋ፣ የሚሠራውም በሥጋ ከኾነ፤ "መንፈሳዊ አገልግሎት" ማለት አይቻልም።

፫፤ አገልግሎቱ፦ በትህትና ከኾነ ነው። ከትዕቢት፣ ከሥልጣን፣ ከክብር፤ እነዚህን ከመሳሰሉት ነገሮች የራቀ ከኾነና በትህትናና ራስን ዝቅ በማድረግ የሚደረግ ከኾነ ነው፤ ይኼ ነው "መንፈሳዊ አገልግሎት" ማለት የሚቻለው። "መንፈሳዊ አገልግሎት" ምድራዊ ክብርን የሚያመጣ፣ ምድራዊ ሥልጣንን የሚያመጣና በምድር ሠዎችን በጣም ከፍ የሚያደርጋቸው ከኾነ "መንፈሳዊ አገልግሎት" መኾን አይችልም። "መንፈሳዊ አገልግሎት" ኾኖ ቢጀመር እንኳን "መንፈሳዊ አገልግሎት" ኾኖ አያልቅም።

፬፤ አገልግሎቱ፦ መሥዋዕትነት ካለበት ነው፤ "መንፈሳዊ አገልግሎት" አገልግሎት የሚባለው። የሚያገለግለው ሠው እራሱ መሥዋዕት እየኾነ የሚያገለግለው ከኾነ ነው። ሌላውን እየሰዋ የሚያገለግለው ከኾነ፣ ወይም ደግሞ ምንም ዐይነት መሥዋዕትነት የማይከፈልበት ከኾነ አገልግሎቱ፦ "መንፈሳዊ አገልግሎት" ነው ማለት አይቻልም። አንድን አገልግሎት፦ "መንፈሳዊ አገልግሎት" ነው የሚያሰኙት እነዚህ አራት ነገሮች ናቸው።

         "መንፈሳዊ አገልግሎት" በሚል (በሰባኪ ወንጌል ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ) በዲ/ ዳንኤል ክብረት የተሰጠ መንፈሳዊ ትምህርተ ወንጌል ሰምተውና  አዳምጠው፤ ስጋዎትንና ነፍሶትን ይመግቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ስም ተጋብዘዋል።

         እግዚአብሔር አምላክ፦ ለወንድማችን ቃለ ሕይወትን ያሰማልን፤ መንግሥተ ሠማያት ያውርስልን። አሜን!

Wednesday, June 18, 2014

"ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን ዓለምም በሞላው በክፉው እንደ ተያዘ እናውቃለን።" /፩ኛ ዮሐ ፭፥፲፱/



(በ፰//፳፻፮ / [15/6/2014 EC] በጣሊያን ሮማ ከተማ፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ፥ የደብረ ከነዓን ቅድስት ሥላሴ / ቅጽር ግቢ ካነሳዋቸው ፎቶዎች።)

ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ በአንደኛው መልእክት በምዕራፍ አንድ ቁጥር አስራ ዘጠኝ ላይ እንዲህ ይላል፦ "ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን ዓለምም በሞላው በክፉው እንደ ተያዘ እናውቃለን።" /፩ኛ ዮሐ ፭፥፲፱/

አምላካችንና መድኃኒታችን፣ መድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ፣ በዚህ ዓለም ላይ በነበረበት በሥጋ ወራት፤ "የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ" /፩ኛ ዮሐ ፫፥፱/ ይህ የተገለጠው፥ አምላክና መድኃኒት ነው። አልፋና ኦሜጋ ነው፣ አልፋና ዖሜጋ፥ ፊተኛውና ኋለኛው ነው፣ መጀመሪያውና መጨረሻው እርሱ ነው፤ እኔ ነኝም ይላል። /ራእ ፳፪፥፳፫/ እርሱ ከዳዊት ዘር የተወለደው፦ የእግዚአብሔር ልጅ፣ የድንግል ማርያም ልጅ፣ አማኑኤል የተባለው፤ እርሱ መድኃኒትና ፈዋሽ፤ ለዓለም የተሰዋ በግ ነው።

ይኼ ሥም፥ አጋንት የሚንቀጠቀጡበት፣ ኃያላን በረዓድ የሚርበተበቱበት፣ ነገሥታት ጉልበታቸውን የሚያንበረከኩለት፣ ጥበበኞች መዕባ የሚያቀርቡለት፣ ምላስ ሁሉ የሚያመሰግነው፣ ድንቅ መካር፣ ኃያል አምላክ፣ የዘለዓለም አባት፣ የሠላም አለቃ፣ አማኑኤል፣ ኤልሻዳይ፣ አዶናይ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

"ስለዚህ፥ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ" /፩ኛ ዮሐ ፫፥፱/ ለሠው ልጅ ጠላት የኾነው ርኩስ መንፈስ ቀርቦ፦ "ዲያብሎስም ረጅም ወደ ሆነ ተራራ አውጥቶ የዓለምን መንግሥታት ሁሉ በቅጽበት አሳየው።" ብሎ፤ ዲያብሎስ፥ ራሱን የስልጣን ባለቤት እንደኾነ በመቁጠር፤ ከአምላካችንና ከጌታችን ጋር ስለ ዓለማት ነገሥታት ክብርና ዝና፣ ላልተገባ የክፉ ስግደት እንዲሰግድለት በጠየቀው ጊዜ አምላካችን ክርስቶስ "ለጌታ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻ አምልክ ተብሎ ተጽፎአል" /ሉቃ ፬፥፩-፲፫/ ብሎት፤ የዲብሎስን የተንኮል ሥራ እንዳፈረሰ፣ ርኩስ መንፈስ እንደገሰጸና ለመንፈሳዊ አባቶች ስልጣንን፣ ለእኛ ለምዕመናን አማኝ ደግሞ እንዴት መጽናት እንዳለብን የነፍሳችን መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ በቃል፣ በምግባር፤ አስተምሮናል።

Monday, June 16, 2014

ሃይማኖታዊ የሚመስሉ፥ ኢ-ሃይማኖታዊ፤ ጽንሰ-ሐሳቦችን ማርቀቅ፤ ለምን? (ክፍል ፪)



የ“ሼሪዓ”ው እስልምና ለክርስትና እና ለሌላው ቤተ-ሃይማኖት ያለው አመለካከት በጣም የተዛባና ፍጹፍ የኾነ ጥላቻ ነው። “ሼሪዓ”ው፥ ያስከተላቸው፣ እያስከተለ ያለውና የሚያስከትላቸው መዘዞች ብዙ ናቸው፤ ይኼንንም የምለው እንዲሁ ከመሬት ተነስቼ አይደለም። “ሼሪዓ”ው እስልምና የሃይማኖት ሊቃውንቶቻቸው ዘንድ ስለ ክርስትና፦ የሚጽፉት፣ የሚናገሩት፣ እንዲሁም አጠቃላይ በሌላ ቤቴ-ሃይማኖቶች ላይ ያላቸው አስተምህሮ መንፈሳዊነት አይታይባቸውም። ለዚህም ማስረጃ ይኾነኝ ዘንድ፦ የ“ሼሪዓ”ው አፍቅሪያን ግለሰቦችና ቡድኖች፥ የሌላ ቤተ-ሃይማኖት ማየት ያስጠላቸዋል፣ ይቀፋቸውማል።[፭] በዕንባና በለቅሶ፥ በታላቅም ጩኧት እየጮኡ የሳውዲው ዋሀቢ ሰባኪ፥ ክርስቲያኖችንና አይሁዶችን የሚረግም ከሱራት ቁራን እየጠቀሱ በስሜት ተውጦ ሲያለቅሱ እንደነበር [፮] እና  “ሼሪዓ”ው እስልምና አፍቃርያን ቡድኖች፤ በክርስቲያኖች ቤተ-ሃይማኖቶች ላይ የቃጠሎ፣ በክርስቲያን አማኞች ላይ ደግሞ፥ የትንኮሳ፣ የማሰቃየት፣ የመደብደብ፣ የመግደልና ከቀዬ የማባረር ተልኳቸውን ሲፈጽሙ እንዳየን፤ የቅርብ ጊዜ ታሪካችን ነው። [፯]

የፖለቲካ ሠዎች የተባሉት፦ እነ አቶ ጀዋር መሐመድ እና የፖለቲካ አጋሮቻቸው፤ የፖለካ ሰዎስለው ለመታየክረው ነበር። ሃይማኖታዊያን ከሚመስሉ፥ ከኢ-ሃይማኖታዊ ከኾኑ ግለሰቦችና ቡድኖች ጋራ በማበር፣ የፖለቲካ ጽንሰ-ሐሳቦቻቸውን በማርቀቅና የፖለቲካ ጥላቻ አመልካከታቸውን እስልምና ሃማኖ በመጫን፤ በክርስቲያኖች ላይ የቃላ ጦር ሲሰነዝሩና ልቱ ዐየናቸው ሰማናቸው። የእነ አቶ ጀዋር መሐመድ፥ የፖለቲካ ጽንሰ-ሐሳቦቻቸውንና የጥላቻ አመልካከታቸውን በሙስሊሙን ሕብረተሰብ በመጫን፣ እስልምናና በክርስትና በቤተ-ሃይማኖቶች ላይ ግጭት እንዲፈጠር፣ ሕዝቡ እርስ-በርስ እንዲበላላ፣ ደም መፋሰስ እንዲር፣ እልቂት እንዲነግስ ለማድረግ የነደፉትን የጥላቻ ንድፍ-ሐሳብቸውን ሲዶልቱና ሲያስዶልቱ እጅጉን ታዘብናቸው[፰] ይልቅስ፥ የእነ አቶ ጀዋር መሐመድ፥ የፖለቲካ ጽንሰ-ሐሳቦቻቸውንና የጥላቻ አመልካከታቸውን ወዳጆች ኢትዮጵያዊያን ወንድሞቻችንና ኅህቶቻችን ሙስሊሞችም ሳይቀሩ ነው የተቃወ (ኾንም ያለበ ተቃሞ!)

እነ አቶ ጀዋር መሐመድ እና የፖለቲካ አጋሮቻቸው፤ ድ ቅችናችን የሀገራችን ሕዝበ-ሙስሊሙ ሕብረተሰብ፥ በክርስቲያኖች ላይ በላቻ እንዲነሱ፣ ክርስቲያኖችንን ለማጥፋት፦ "በሜንጫ፥ አንገት አንገታችንን እንዲጨፈጭፉ" የጥላቻ ስብከታቸውን ሰበ እኛ ክርስቲያኖች፥ በታላ ኢትዮጵያ ሀገራችንውቧ ክልላችን በኦሮምያ ላይ እንዳንኖር ህልውችንን ለመሻ ክሩ፣ ሕይ እንር፥ ድራሻችንን ከነ አካቴው እንድንጠፋ የላቻ ስብከታቸውን አስተጋቡ። ሀጅ ነጂብ በተራቸው፦ ''የኢትሕዝብ ህብረተ-ሰእብ ትንሹሚሊ ይኾል፣ዚህ ሚሊን ውስጥ ሰማያ ፐንት (80%) ኦሮሞ ነ,,,,'' ሲሉ ተደምጠዋል። በማከተልም፦ “የቀረው ሃያ ፐርሰንት (20%) የትም ሊደርስ አይችልም ሲሉ እንደተናገሩት ልብ እንበል! እንግዲህ እንደነ አቶ ጆዋር መሐመድ እና የፖለቲካ አጋሮቻቸው ዐይነቶች፤ ኢትዮጵያን ሊያስተዳድሩ ሥልጣን ቢኖራቸውና ቢችሉ ኖሮ የሃይማኖት ነፃነት ምን እንደሚመስል ቡዙ መተንተን አልያም ነብይ መኾን አያስፈልግም።[፱]

Wednesday, June 11, 2014

ሃይማኖታዊ የሚመስሉ፥ ኢ-ሃይማኖታዊ፤ ጽንሰ-ሐሳቦችን ማርቀቅ፤ ለምን? ክፍል ፩


ሃይማኖት ማለት፦ ሠማያዊ ነገርን በመሻት፥ መንግሥተ ሠማያትን ተስፋ በማድረግ፤ የሚኖርበት ማለት ነው። ታዲያ፥ የማንኛውም ሃይማኖተኞች መሪዎች ለሃይማኖት እምነት ተከታዮቻቸው (ለምዕመኖቻቸው) የሚያምኑበትን፥ እምነትና ሃይማኖት በፍቅርና ስለ ፍቅር ሊሰብኩላቸው፣ የሰበኩላቸውንም በልባቸው ውስጥ እንዲታተም ማስተማር አለባቸው። ተስፋ ስለሚያደርጉት ስለ ሠማያዊት መንግሥተ ሠማያት በመናፈቅ ከዓለማዊ ምኞት በጸዳ ኹኔታ አስረግጠው ማስተማር መኾን አለበት!። ለምን ቢሊ፥ የሠው ልጅ በእዚች ምድር እስከሚኖርበት ጊዜ ድረስ፦ ከተወለደበት ቀዬ ወደ ሌላ ቀዬ፣ ከነበረበት ከተማ ወደ ሌላ ከተማ፣ አድጎና ተምሮም የዕውቀር ማዕድ ካወቀባት ሀገር ወደ ሌላ ሀገር ሲሄድ የሚያጋጥሙትና በሕይወቱ የሚከሰቱ ክስተቶች ብዙ ነገሮች አሉʼ። ከክስተቶቹ አንዱ ደግሞ እምነትና ሃይማኖት ነው፤ በዚህ ጊዜ የ“ሃይማኖት፥ የነፃነት ምርጫ” ወደሚለው ክስተት ራሱን ይፈልጋል።

በሀገሩም ይሁን ከሀገሩም ውጭ፤ ባጋጠመው በዚህ የ“ሃይማኖት፥ የነፃነት ምርጫ” ክስተት ፍለጋ ከእናትና ከአባቱ የወረሰው ሃይማኖት ይኹን፣ በተለያየ ምክንያት የተቀበለውን እምነትና ሃይማኖት ይዞ ቢጸና እሰየው ያስብላል። ከእዚህ በተረፈ ሃይማኖቱን በየትኛውም መንገድ ከተማም ውስጥ ይኹን በየትኛውም ሀገር ላይ በሕይወት እስካለ ድረስ እምነቱንና ሃይማኖቱን ሊቀይር ይችላል፤ ወደ ሌላ እምነትና ሃይማኖት ራሱን ቀየረ ማለት የራሱን መንገድ ፈለገ ማለት ነው። የፈለገውን ሃይማኖትና እምነት የመከተል ከአምላክ የተቸረው ልዩ ሥጦታ ነው። ይኼን ሥጦታ ደግሞ የቀድሞ ቤተ-ሃይማኖቱ ከቻለች በድጋሚ አስተምራ በቀድሞው እምነትና ሃይማኖት እንዲጸና ማድረግ አለበዚያ ግን ለየአንዳንዱ ሠው ከአምላክ የተቸረውን የእምነትና የሃይማኖት ነፃነትን በጸጋ መቀበል አለባት።

ቢጣፍጠንም ቢመረንም፦ የሠውን ልጅ የእምነትና የሃይማኖት የነፃነት ምርጫውን ማክበር አለብን! ሊከበርለትም ይገባል!። በእስልምና ሼሪዓግንዚህ የተለየ ነው። የቀድሞውን ሃይማኖቱን ብቻ በመቀየሩ ምክንያት፦ እንደ ማፊያ ቡድኖችና እንደ ወንጀለኛ ድርጅቶች፤ ከዚህ ሃይማኖታዊ ድርጅት ከወጣህና ወደ ሌላ ሃይማኖት ከሄድህ ውርድ-ከራስህ፤ ዐይነት ነገር ይባላል። እንደ ማፊያዎቹ አባባል፦ “ምስጢር ታወጣለህ፣ አልያም ሀገርን ለጠላት አሳልፎ እንደሸጠ” ተቆጥሮ፤ የሞት ፍርድ ይበየንበታል። [፩] ዶ/ር ዛኪር እንዳሉት

የ“ሃይማኖት፥ የነፃነት ምርጫ” ከዶ/ር ዛኪር በፊት የነበሩት የሙስሊሞች መምህራን እንኳን የሠዎችን የእምነት ነፃነትን በመንፈግ እምነቱን ለሚቀይር ከፊቱ ላይ የመቃብር ቁፋሮ እንዳለ ያመላክታሉ። እንደተናገሩትም፥ እንደዚህ እያሉና እያስባሉ፦ “አንገትህን በሠይፍ እንቀላለን፣ በሕይወት የመኖርህ ህልውና ነገር ያከትማል፣ አትኖራትም፣ ንብረትና ልጆችህ ለሃይማኖታዊ ድርጅቱ” በማለት ጊዜ ያለፈበትና ሃይማኖቱን ለዘላቂያዊ በፖለቲካ ለማካሄድ የነደፉት፦ ሃይማኖታዊ የሚመስሉ፥ ኢ-ሃይማኖታዊ፤ ጽንሰ-ሐሳብቦችን ማርቀቅ ለምን? እንደፈለ ሙስሊሙ ሕብረተሰብ እንዴት እስከዛሬ አይረዳውም!!!።

Wednesday, June 4, 2014

“እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ።” /ዮሐ ፰፥፵፬/



የእግዚአብሔር ቃል ክብር ለሚገባው ክብር መስጠት እዳለብን ያስተምረና፤ /ሮሜ ፲፫፥፯/ ቢኾንም ግን አንዳንድ የፕሮቴስታንቶች ፓስተሮች (የተቃዋሚ አገልጋዮች) ይኼንን አምላካዊ ቃል ወደ ጎን በመተው የራሳቸውን ሥጋዊ ምኞቶቻቸው እንዳዛዘቸው እየፈጸሙና እያስፈጸሙ ነው። አባታችሁ ዲያብሎስ ከመፈሳ ይልቅ ምኞት ላሳወራቸው፤ ምኞታቸውን የተከተልጉትንና የኙትን ነገሮ ሁሉተ-ክርስቲኒቷ ላይ እጃቸውን በኃይል በመጫን ያሻቸውን ማድረ ጀምረዋል።

ቢኾንም ግን ከመጀመርያው ጀምሮ ፕሮቴስታንቶች፥ ከካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን ሲያፈነግጡ፤ የነበራቸው እምነትና ሃይማኖት ከካቶሊካውያን የወረሱትን መሠረታዊ የካቶሊካውያንን ሥርዓት በመያዝ ነበር። ሉተር፥ ከካቶሊካውያን ያፈነገጠበት ዋናው ምክንያት፦ ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን በወቅቱ ለአንዳንድ ነገሮች የገንዘብ ማሰባሰቢያ ስለፈለገች ስለነበር  ያዘጋጀችውን ትኬት “የመንግሥተ ሠማያት የመግቢያ ትኬት” ነው፤ ትኬቱን ግዙ እያለችና እያስባለች በነበረበት ወቅት በሉተር አማካኝነት ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን ተቃውሞ  ገጠማት። ይኼም ተቃውሞ እየበረታና እያየለ ኼዶ፤ ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን የራሷን ልጆች የነበሩትን እነ ሉተርን በማግለልና እነ ሉተርም የራሳቸውን ተቃውሞ በሀገሩ ላይ በተለያዩ  ከተሞች የሚገኙ የቀድሞ የካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን በሮች ላይ የተቃውሞውን ሐሳቦቹን ጽፎ ለጥፎ ነበር።

ይኹን እንጂ፥ የፕሮቴስታንቶች እምነትና ሃይማኖት እንደዚህ ከመቀየሩ በፊት፦ ለመድኃኒታችንና ለአምላካችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ያላቸውን ጥልቅ ፍቅር፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱሳንና ለሰማህታት ባዘዛቸው መንገድ፥ ለእናቱ ለቅድስት ድንግል ማርያም፣ ለቅዱሳኑ፣ በአጠቃላይ ከካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን የወረሱትን ሃይማኖታና ባህላዊ፣ ትውፊትና ቅዱሳት መጽሐፍቶቻቸውን እስከተወሰነ  ጊዜያት ድረስ ይጠቀሙበት ነበር።

ከዛ በኋላ የተነሱ ልዩ ልዩ የፕሮቴስታንቶች መሪዎችና ፓስተሮች የተዛባ አስተሳሰባቸውን በመርጨት፦ ለድንግል ማርያምና ለቅዱሳን፣ ለሰማህታትና ለፃድቃን፣ ለደናግልና ለአባቶች፤ እንዲሁም ደግሞ ለቅዱሳት መጽሐፍትና ለቅዱሳት ሥዕላት፤ ማንቋሸሽ፣ ማብጠልጠል፤ ጥቅም አልባ ማድረግ፤ ከምዕመናኑ፥ ልቦናና ኅሊና ፍቆ ማውጣት፤ የነደፉት ንድፈ-ሐሳባቸውን በመጫን ያላቸውን ጥላቻ ቀስ በቀስ ቀጠሉበት።

ለእምነት የሚከፈል ዋጋ!!!

(ሪፖርተር፥ ግንት ፳፯/፳፻፮ ዓ/ም 04 June 2014)

‹‹እምነትን ማዛባት፤ ጭካኔ ተሞልቶበታል የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሮን

‹‹ጉዳዩ ውስብስብ ነው፣ ጎሳንና ማኅበራዊ ሕይወትን ይነካካል፤ በመሆኑም የሞት ፍርዱ ተፈጻሚ አይሆንም›› የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትሩ አብዱላህ አል አዝራቅ

ከእስልምና ወደ ሌላ ዕምነት መቀየር ፍፁም የተከለከለ ነው፡፡ ዕምነት የሚፀናውም በአባት ነው፡፡ ልጆች ከሙስሊም አባት ከተወለዱ የእናታቸው ዕምነት እስልምና ካልሆነ በስተቀር የፍላጎታቸውን ዕምነት መከተል አይችሉም፡፡

ለዕምነት የሚከፈል 70 በመቶ በላይ ሕዝቧ የእስልምና ዕምነት ተከታይ በሆነባት ሱዳን የሌላ ዕምነት ተከታይም ቢሆን ትዳሩን ሲመሠርት የሚዳኘው በእስልምና ሕግ ነው፡፡ ክርስቲያን ሆኖ ሙስሊሟን ቢያገባ ልጁን የማሳደግ መብት አይኖረውም፡፡ ሚስቲቱም ሃይማኖቱ የሚያዛትን እንደጣሰችና ዕምነት እንደቀየረች ተቆጥራ በወንጀል ሕግ ትዳኛለች፡፡

በሱዳን የእስልምና ሃይማኖትን በሌላ ዕምነት የቀየረ የሚፈረድበት ሞት ነው፡፡ በአፍጋኒስታንና በሌሎችም የእስልምና መንግሥት ያላቸው አገሮች እስልምናን ከመቀየር ጋር በተያያዘ የሚወስኑት የሞት ፍርድ ከሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ በሙስሊም አስተምርሆ ውስጥ ሆነው ባህላዊ አካሄድ ነው በማለት ቅጣቱ ሞት መሆን እንደሌለበት ከሚናገሩ፣ እንዲሁም ከሌሎች ዕምነት ተቋማት ጋር ሁሌም እንዳወዛገባቸው ነው፡፡

በመንግሥት ተቋማት ደረጃ ብቻም ሳይሆን የእስልምና እምነቱን የቀየረ ወይም የቀየረች ሲገኝ ወይም ስትገኝ በመደበኛ ፍርድ ቤት ደረጃ ሳይደርሱ በአካባቢያቸው ነዋሪዎች ፍርዱ የሚፈጸምባቸውም ቀላል አይደሉም፡፡ በተለይ ደግሞ ሴቶች የብትሩ ሰለባዎች ናቸው፡፡

ሰሞኑን በሱዳን ካርቱም አከራካሪና አነጋጋሪ ሆኖ የከረመው አጀንዳም ይኼው ነው፡፡ ከኢትዮጵያዊት ክርስቲያን እናትና ከሱዳናዊ ሙስሊም አባት የተወለደችው ማርያም ያህያ ኢብራሂም ክርስቲያን ማግባቷ ከስህተት ተቆጥሮባት እስር ቤት እንድትገባ፣ 100 ጅራፍ እንድትገረፍና በሞት እንድትቀጣ እንዲወሰን ምክንያት ሆኖባታል፡፡

Sunday, June 1, 2014

"ጠንቋይና አስጠንቋይ" በመልአከ ሰላም ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራው


,,, እንዲህ የሚያስጨክን፥ የማይገባ ሥራ የሚያሰራ ሰይጣን ነው። በየ-አንዳንዱ ጎጆ (መኖርያ ቤት) ውስጥ ቢገባ ብዙ ጉድ አለ! ተስፋውን በጥንቆላ ላይ አድርጎ የሚኖር፣ ጠንቋዩ፥ በመከረው ምክር የሚመላለስ፣ ያንን በይፈጽም እንደው ዕለቱን መሬት-ተከፍታ የምትውጠው የሚመስለው አለ። በጥንቆላ፣ በመተት፣ በአስማት፤ ወገኖቻቸውን የሚያሳብዱ፣ ወገኖቻቸውን የሚገድሉ፣ ወገኖቻቸውን የሚያፈዙ፤ ጥቂት አይደሉም።

እገሌ እኮ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበረ፤ አሁን ግን ጨርቁን ጥሎ የሚኼደው። ምን ነካው? "ጓደኛው ነው ያቀመሰው አሉ" ይባላል። እገሌ እኮ ጥሩ ደሞዝ ነበረ፣ እንዲህ ዐይነት ቦታ ይሠራ ነበር፤ አሁን እንዲህ ከንቱ ኾኖ ቀረ። ምን ኾነ? "ጓደኛው ነው እንዲህ ያደረገው" ይባላል። እገሌ እኮ እንዴት ያለ ነጋዴ ነበረ፣ ቢጠሩት የማይሰማ፤ አሁን ግን ከንቱ ኾኖ ቀረ። ምን ኾነ ታዲያ? "አይ፥ በንግዱ የቀኑበት ሠዎች ናቸው እንዲህ ያደረጉበት" ይኼንን ነው የምንሰማው።

በአካባቢው፥ በመንደሩ፤ የሚነገረው ይኼ ነው። ጠንቋይ፥ ቤት የሚያድረው ሕዝብ፣ ቃልቻ፥ ቤት የሚያድረው ሕዝብ፤ ብዛቱ፥ ቁጥር-ስፍር የለውም። ምንድነ ነው የሚሻለን ታዲያ? የእግዚአብሔርን ቃል፥ አልሰማንም እንዳንል፤ ሰምተናል! ተአምራቱን፥ አላየንም እንዳንል ዐይተናል! ግን ሰምተን እንዳልሰማን ኾንን፣ ዐይተን እንዳላየን ኾንን! የአንዳችንም ሕይወት ሲለወጥ ዐይታይም።

ተማሪው፥ "ትምህርት እምቢ አለኝ" ሲል፤ እንደው፦ "ጠንቋይ ቤት ሂድ ጠንቋዩ ይነግርሃል፤ እቃልቻው ቤት ብትሄድ ይነግርሃል" ይባላል፤ እውነት መስሎት ይሄዳል። ነጋዴውም፥ "ንግድ እምቢ አለኝ ምን ማድረግ ይሻለኛል" ሲል፤ "እጠንቋዩ ጋር ብትሄድ፤ እቃልቻው ቤት ብትሄድ" ይባላል። መሪ፥ መካሪ አለው እርሱም (ርኩስ የሰይጣኑን መንፈስ) ሥራ፥ ፈልጌ፣ ፈልጌ አጣኹ፤ ምን ይሻለኛል? ሲል፤ "እጠንቋዩ ጋር ብትሄድ፣ እቃልቻው ቤት ብትሄድ፤ ሥራ ታገኛለህ" ይኼ ደካማ ሕዝብ ሥጋዊ ፍላጎቱን ለሟሟላት ሲል፥ ሃይማኖቱን ሽጦ፣ ለውጦ፤ ከአምልኮተ እግዚአብሔር ሲንሸራተት፣ ሲያፈገፍግ ይታያል።

እንደው፥ ዘመኑ ዓመተ ምዕረት ኾኖ፤ እግዚአብሔር፥ ኃጢያት፣ በደላችንን ሸፍኖልን ነው እንጂ! የእየ-አንዳንዳችን ኃጢያት በየግንባራችን የሚፃፍ፣ የሚገለጥ ቢኾን ኖሮ ከእኔ ጀምሮ ኹላችንንም ብንኾን ከዚህ ቦታ ባልተገኘንም ነበር! እንደውም፥ ጥንቆላ የተስፋፋበት ዘመን ነው። በየ-ጋዜጦች ላይ የምናነበው፤ ጥንቆላ አይደለ? ወይስ የእግዚአብሔር ነቢያት ነው የፃፉልን? ትንቢተ ማን እንበለው? ግራ-የሚገባ (የሚያጭበረብር) ነገር እኮ ነው።