Friday, April 3, 2015

ክብር መስጠት፤ ቀሲስ ሰሎሞን ሙሉጌታ


                               በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

ሰዎችን ማክበር ትኩረታቸውን ለማግኘት ይረዳናል። እግዚአብሔርን የምናምንና ስላመነውም ምስክርነት የምንሰጥ ሰዎች ሁሉ ሁሉን ማክበር ይጠበቅብናል። ሽማግሌም ሆነ ወጣት፣ የታመመ ሆነ ጤነኛ፤ ድሃም ሆነ ባለጠጋ፤ የተማረም ሆነ ያልተማረ፤ ወንድም ሆነ ሴት፤ ጻድቅም ሆነ ኃጥእ ሁሉን ማክበር ይጠበቅብናል፡፡ እነዚህ ሰዎች አስቀድሞ የነበራቸው ልምድ ምንም ይሁን ምን፣ አመለካከታቸውና ሥነ ምግባራቸውም መልካምም ይሁን መጥፎ እንድናከብራቸው ይጠበቅብናል።

ሰዎችን የምናከብራቸው በተለያዩ ምክንያቶች ነው፤ በቅድሚያ እግዚአብሔር በአምሳሉና በአርአያው ስለ ፈጠራቸው እናከብራቸዋለን። ስናከብራቸውም ያከበርነው የተፈጠሩበትን የእግዚአብሔርን አምሳልና አርአያ መሆኑን ማወቅ ይጠበቅብናል። ሰዎችን የምናከብርበት ሁለተኛው ምክንያት እግዚአብሔር ልጁን ለሰው ዘር ሁሉ መሥዋዕት ይሆን ዘንድ ስለሰጠ ነው። ይህን የማዳን ሥራ እግዚአብሔር ከፈጸመላቸው ታላቅ መሥዋዕትነትም ከከፈለላቸው ታዲያ ቢያንስ ይህ የተደረገላቸውን ሰዎች ማክበር አይጠበቅብንም ይሆን? ሦስተኛው ሰው ምንም ያህል ክፋት ወይም መጥፎነት ቢኖርበትም በውስጡ ግን መልካምነት ስለሚገኝበት ሰውን ልናከብረው ይገባል።

ሰውን ማክበር በውስጣችን የሚገኘውን መልካምነት መቀስቀሻ መሣሪያ ነው፤ ይህም ሰው ክርክርንና ራሱን መከላከልን ትቶ ለነገሮች ጆሮ ሰጥቶ ለመስማት ያበቃዋል። ማክበር ሰውን ሳናስገድድና ሳናስጨንቅ ለመስማት የሚችልበት ነጻነት እንድንሰጠውና በእግዚአብሔር ጸጋ በመታመን ወደ ምሥራቹ ወንጌል ለመጥራት ይረዳናል፤ ጥሪያችንን ካስተላለፍን በኋላ የምሥራቹን ወንጌል መቀበልም ሆነ አለመቀበል ግን የእያንዳንዱ ሰው ፈንታ ነው።

ክብር መስጠት ስንል የሰው የግል መብቱን ነፃነቱንና ምስጢሩንም ማክበርንም ያካትታል፤ ስለዚህ ምንም በቅርበት የምናውቃቸው እንኳ ብንሆን ሰዎችን ወደ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖታችን ለማቅረብ የምናደርገው ጥረት የሚሳካው በግኑኝነታችን ወይም በንግግራችን ወቅት ክብር ሰጥተን በምንጓዘው መንገድ ርቀት ነው። ክብር መስጠት የሰውን ስሜት የሚጎዱ ቃላቶችን አለመጠቀምን ያካትታል። የሰዎችን ባሕል፣ እሴቶቻቸውን፣ የቀደመ ታሪካቸውን በአግባብ መረዳትና ማወቅ ክብራቸውን የሚጎዳ ስህተት ከመሥራት ይታደገናል። ይህም ማስተዋል የተሞላበት አካሄድ እግዚአብሔር በመንገዱ እንዲመራን ለመጠየቅና ለመጸለይ ይረዳናል፤ ምንም ብናውቅ ሰውን ሊያስቀይሙ አጋጣሚዎች ሊፈጠሩ ይችላሉና።

Friday, March 13, 2015

እንደገና ወደ ግብጽ መኼድ፦ ሊቀ ሊቃውንት አለቃ አያሌው ታምሩ



በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አመራር ላይ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በተደጋጋሚ የተከሰቱትን የሃይማኖት ትምህርትና የሥርዓት መበላሸት በማስመልከት የቤተ ክርስቲያኒቱ የሊቃውንት ጉባኤ ሰብሳቢ የነበሩት አለቃ አያሌው ታምሩ ችግሩ ሥር ሳይሰድ ገና ከጅምሩ እንዲታረም ማሳሰቢያና ተማጽኖ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ተደጋጋሚ ተማጽኖ አቅርበው ነበር። ነገር ግን ጥያቄአቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ዘንድ በቸልታ በመታየቱ ምክንያት፤ አለቃ አያሌው ታምሩ ባላቸው ከፍተኛ ሥልጣንና ኃላፊነት፤ በቤተ ክርስቲያን ላይ ዐመጽ የሚፈጽሙትን ፓትርያርኩንና ተከታዮቻቸውን ማውገዛቸው ይታወቃል። ቃለ ግዝታቸው በመጀመሪያ የወጣው ሰኔ ፳፯ ቀን ፲፱፻፹፰ / «መብሩክ» ጋዜጣ ላይ ነበር። ሙሉውን ቃለ ውግዘት ለማንበብ ከዚህ ይጫኑ

አባታችን ይህን ቃለ ውግዘት ካስተላለፉበት ጊዜ ጀምሮ፤ ከምእመናንና ከተለያዩ ክፍሎች ውግዘቱን አስመልክቶ የተለያዩ ጥያቄዎች በቃልና በጽሑፍ፥፣ እንዲሁም በተለያዩ ጋዜጦች ላይ የቀረቡላቸው ሲሆን፤ ለቀረቡት ጥያቄዎችም ተገቢ የሆኑ ምላሾችን ሰጥተዋል ሰጥተዋል። በተለያዩ ጊዜዎች ከቀረቡላቸው ጥያቄዎች መካከል በ፲፱፻፺ / ብዙ ምእመናን በመኖሪያ ቤታቸው ተገኝተው በጋራ ያቀረቡላቸው ሲሆን፤ ከእነዚህ ጥያቄዎች መካከል አንዱ "በዚህ ውግዘት መካከል በእርስዎ ወይም በሳቸው መካከል የመለየት ባሕርይ ቢኖር ውግዘቱ እንደ ታሰረ ነው ወይስ እንደ ተፈታ ነው የሚቆየው? ውግዘቱን ማን ይፈታዋል? እስከ መቼ ድረስ ነው ውግዘቱ የሚቆየው?" የሚል ሲሆን፤ ክቡር አባታችን የሚከተለውን ምላሽ ሰጥተው ነበር።

Monday, February 16, 2015

ስለ መካ ከተማ መያዝ (መሸነፍ)፦


(ከአስራ  ስምንት ዓመት በታች ማንበብ አይፈቀድም!)

            ሙሐመድም . . . ከዚህም ሌላ መካን በጦር ኃይል ለመያዝ ያደረገው ሃሳብ የተቀደሰ ስፍራ ነው፤ ስለ ሃይማኖት ግዴታ መካን መያዝ አለብን ብሎ ለተከታዮቹ አስረዳ። «መካውያን መካ ገብተን እንሰግድ ዘንድ ያልፈቀዱልን እንደኾነ ምን ማድረግ ይገባናል» ብለው ተከታዮቹ ቢጠይቁት፤ «እኔ የመጨረሻው ነቢይ፥ ሰይፌን ጨብጬ ተላክሁ፣ ሰይፉም፥ የመንግሥተ  ሠማያና የገሃነም መክፈቻ ነው። ስለ ሃይማኖት ሲሊ የሚመዝዙት ሰይፍ ዋጋ ያገኙበታል።» ሲል ሙሐመድ መለሰላቸው።

           . . . ሙሐመድ በዕድሜው እያረጀ ሄደ፣ እንደ ልቡ ለመራመድ አልደፈረም። የደም ሥሮቹም ደክመው ነበር። በአረብ ሃገር፥ ነቢይነቱንና መሪነቱ በመታወቁ መጠን፣ ዓለም በመላ የእስላም ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ግዛት ትኾን ዘንድ አለመ። መዲና ላይ የጦር ኃይሉን እንደ አደራጀና እንዳጎለመሰ ሁሉ በሌሎች ሃገሮችም የእስላምን ሃይማኖት የሚዘረጉትንና የሚያስፋፉትን የክብር መልክተኞችን ማደራጀት ጀመረ። እንዲህ ሲልም ለውጭ ሃገር መንግሥታት መሪዎች ጻፈ፤ ለሮም ቄሣር የጻፈው ደብዳቤ ከዚህ በታች የሚገኘው (የሚነበበው) ነው። ለሌሎችም ነገሥታት ሁሉ የጻፋቸው ደብዳቤዎች እንዲሁ ያሉ ነበሩ፦

Sunday, February 8, 2015

ንግሥት ሳባ፦

ንግሥት አዜብ፥ የንጉሥ ሠለሞንን ጥበብን ለማየትና ለመስማት እንደተገናኘችና ከሃገራችን የሚገኘውን አልማዝና ወርቅ እጅ መንሻ ሥጦታ እንዳበረከተችለት፤ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦ "ለንጉሡም መቶ ሃያ መክሊት ወርቅ፣ እጅግም ብዙ ሽቱ፣ የከበረም ዕንቍ ሰጠችው፤ የሳባ ንግሥት፥ ለንጉሡ ለሠሎሞን እንደ ሰጠችው ያለየሽቱ ብዛት ከዚያ ወዲያ አልመጣም ነበር።" (፩ኛ ነገ ፲፥፩-፲፫፤ ፪ኛ ዜና ፱፥፩-፲፪፤ ማቴ ፲፪፥፵፪፤ ሉቃ ፲፩፥፴፩)