Wednesday, May 14, 2014

የሠው፥ ልዩ ዘር ኧረ ወዴት አለ?


ገበሬው አውድማው እህል ማረስ፤
አፈሩ ተኰተዋ እንዲለስለስ፤
ሩን ይዘራዋል በስብሶ እንዲፈርስ፤
ቃያሲያፈራ ማሳው ሲደርስ።

በዘራው የእህል በዓይነት
እዪ ሐሴት ያደርግ ገበሬው ሲደሰት

አንዳችን ስለ አንዳችን፣ በፍቅር ዓለም ከተዋደድን፤
ልዩነት ከየት ይመጣል፣ በሕይወት ሥር ከሰደድን፤
ዘር ቆጠራ፥ ለእህል እንጂ! ለእኛ ለሠዎች አይኹን፤
በፍቅርና በአንድነት መኖር፣ ቆየን ከተለማመደን።

ገበሬው በዘራው የእህል ዘር ፍሬ መደሰት፤
ያለʼውን፥ አንድነትና ልዩነቱን እንመልከት።

እንዳንኾን፥ ታሪካን ለማፍረስ፤
በልባችን፥ የፍቅር ዘርን እንረስ፤
ኅሊናችን፥ ለሌላው ሲለሰልስ፤
እንደሰታለን ፍሬው ሲደርስ።

የእህል ዘር፥ ዓይነቱ ብዙ
የሠው ዘሩ፥ ኧረ ወዴት ?

አፋልጉልኝ፥ የእከሌ ዘር ነኝ ያላለ፤
ይኼ ነው! ልዩ ሠው ለፍቅር የዋለ፤
ፍቅር፥ መተሳሰብና አንድነት ካለ፤
የሠው፥ ልዩ ዘር ኧረ ወዴት አለ?

ለሃገ አንድነት፥ ኹሌ የሚናፍቀው፤
ባንዲራዋን፥ በፍቅር የሚመለከተው። 
                 
ራሱን ጥቅም ይልቅ ለአንዲት እምዬ ኢትችን፤                                                    
የወንዙና የሸንተረሩን ጐጥ ብቻ ያልተመለከተውን፤
ሳዩኝ ይኼን ሠው፥ኢት ዋጋ የከፈለውን፤
ይኼ! ለ ሃገ አንድነትን የሚሻውን።      

በህብረ-ቀለማት ፍቅሩ የረሰረሰና ለሃገ
ለኢትዮጵያችን፥ ይኼ ሠው ታላ

ወዳጄ ሆይ፦ ራስህን በመውደድህ፤
ትኖራለህ፥ ሌላውንም ታከብራለህ፤
ለሃገርህም ሠላምና ፍቅርን ትሻለህ፤
ግርማና ክብርበነቷንም ትናፍቃለህ።

ክብርን ለማግኘት ተቀይሶ የዋለ
የሠው፥ ልዩ ዘር ኧረ ወዴት አለ?

እኔ፥ ከዚህ ዘር ነኝ እንዳንባባል፤
ኹላችን ከአዳም ዘር ተወልደናል፤
ከማይጠፋው ዘር ተገኝተናል፤
ክርስቶስ ፍቅርን አስተምሮናል።

(//፳፻፮ /)

No comments:

Post a Comment