Showing posts with label ሥነ-ግጥም. Show all posts
Showing posts with label ሥነ-ግጥም. Show all posts

Friday, December 19, 2014

የሰይጣን አመሉና ጉዞ



  የሰይጣን አመሉ

ሰይጣን አምላክ እንዳለ ያምናል ይንቀጠቅጥማል፤
ቢኾንም ግን፥ የጌታን ቸርነቱንና ኃይሉን ይክዳል፤
ሰይጣን ለአመሉ፥ ከቅዱስ ቃሉ ጥቅስ ይጠቅሳል፤
የብርሃን መልአክ እንዲመስል፥ ራሱን ይለውጣል።

የሰይጣን ጉዞ

ክርስቶስን፥ የባህሪይ አምላክነት ያስክድሃል፤
ድንግል ማርያም ፍቅር፥ ሊያርቅህ ይኳትናል፤
ከቅዱስ መልአክት ተራዳኢነት እቅፍ ያስርቅሃል፤
በመንፈሳዊ ሕይወት፥ እንዳትጎለብት ይጎስምሃል።

የቅዱሳን አበው ተጋድሎ፦ እንደ-ኢምኒት አድርጎ ያሳይሃል፤
ዶሮ ሁለት ጊዜ ሳይጮኽ፥ ሦስት ጊዜ አምላክህን ያስክድሃል፤

የቅዱሳን ምልጃ፥ እንኳን በአጸደ ነፍስ በአጸደ ሥጋ የለም ይልሃል፤
ለምዕመናን ተስፋ አስቆራጭ እንድትኾን በቅዱስ ስፍራ ይሾምሃል፤
ከእውነታኛው የሃይማኖት መንገድና ኢየሱስ ጥልቅ ፍቅር ያስርቅሃል፤
አንዴ ከመንገዱ ፍቅቅ ስላደረገኽ በዓለማዊ ዕይታና ምኞት ይዘፍቅሃል።

ፆም ፀሎት ሥግደት እንዳታደርግ ይወተውትሃል፤
በሥጋ ወደሙ እንዳትከብር እንከን ይፈጥርብሃል።

በመጨረሻም፥ በራስህ እንድትታበይ ያደርግሃል፤
በአንድ ምላስ፦ እውነተኛው ቃልህን ያሳጥፍሃል፤
እኔስ ከማንና ከማን አንሳለው እንድትል ያነሳሳሃል፤
ባደፈ ልብስ እግዚአብሔር ፊት ሊከስህ ይቆማል።

(ኃይለ ኢየሱስ //፳፻፯)

Monday, December 1, 2014

ሕይወታችሁን አጣፍጡ!



የሕይወት ውኃው ለማግኘት፥ ከእንስቶች የለያት፣
የሕይወት ውኃ ኾነና፥ እርሷን ምንጩ አደረጋት፣
ማንም ለመርካት ቢፈልግ፣ ድንግልን ንጉሥ ሾማት፣
በእቅፏ እንድታቅፈው፥ እናቱ እንድትኾን የመረጣት።

ክርስቶስን ለማግኘት፥ እስኪ ቅዱና ጠጡ፤
ከድንግል ዘር፥ ሕይወታችሁን አጣፍጡ!

ከምንጩ አጥልቁ፥ መቅጃችሁን ከጉድጓዱ፤
ይገባችኋል የእናቱን ፍቅር፥ የናቃት ሲሰግድ፣
የእርሱን እፎይታ ታገኛላችሁ ከጥልቁ ስትቀዱ፣
ያኔ ሕይወታችሁን ስታጣፍጡ በፍቅሯ ስትነዱ።

(ህዳር ፳፪/ ፳፻፯ /)

Wednesday, May 14, 2014

የሠው፥ ልዩ ዘር ኧረ ወዴት አለ?


ገበሬው አውድማው እህል ማረስ፤
አፈሩ ተኰተዋ እንዲለስለስ፤
ሩን ይዘራዋል በስብሶ እንዲፈርስ፤
ቃያሲያፈራ ማሳው ሲደርስ።

በዘራው የእህል በዓይነት
እዪ ሐሴት ያደርግ ገበሬው ሲደሰት

አንዳችን ስለ አንዳችን፣ በፍቅር ዓለም ከተዋደድን፤
ልዩነት ከየት ይመጣል፣ በሕይወት ሥር ከሰደድን፤
ዘር ቆጠራ፥ ለእህል እንጂ! ለእኛ ለሠዎች አይኹን፤
በፍቅርና በአንድነት መኖር፣ ቆየን ከተለማመደን።

ገበሬው በዘራው የእህል ዘር ፍሬ መደሰት፤
ያለʼውን፥ አንድነትና ልዩነቱን እንመልከት።

እንዳንኾን፥ ታሪካን ለማፍረስ፤
በልባችን፥ የፍቅር ዘርን እንረስ፤
ኅሊናችን፥ ለሌላው ሲለሰልስ፤
እንደሰታለን ፍሬው ሲደርስ።

የእህል ዘር፥ ዓይነቱ ብዙ
የሠው ዘሩ፥ ኧረ ወዴት ?

አፋልጉልኝ፥ የእከሌ ዘር ነኝ ያላለ፤
ይኼ ነው! ልዩ ሠው ለፍቅር የዋለ፤
ፍቅር፥ መተሳሰብና አንድነት ካለ፤
የሠው፥ ልዩ ዘር ኧረ ወዴት አለ?

ለሃገ አንድነት፥ ኹሌ የሚናፍቀው፤
ባንዲራዋን፥ በፍቅር የሚመለከተው። 
                 
ራሱን ጥቅም ይልቅ ለአንዲት እምዬ ኢትችን፤                                                    
የወንዙና የሸንተረሩን ጐጥ ብቻ ያልተመለከተውን፤
ሳዩኝ ይኼን ሠው፥ኢት ዋጋ የከፈለውን፤
ይኼ! ለ ሃገ አንድነትን የሚሻውን።      

በህብረ-ቀለማት ፍቅሩ የረሰረሰና ለሃገ
ለኢትዮጵያችን፥ ይኼ ሠው ታላ

ወዳጄ ሆይ፦ ራስህን በመውደድህ፤
ትኖራለህ፥ ሌላውንም ታከብራለህ፤
ለሃገርህም ሠላምና ፍቅርን ትሻለህ፤
ግርማና ክብርበነቷንም ትናፍቃለህ።

ክብርን ለማግኘት ተቀይሶ የዋለ
የሠው፥ ልዩ ዘር ኧረ ወዴት አለ?

እኔ፥ ከዚህ ዘር ነኝ እንዳንባባል፤
ኹላችን ከአዳም ዘር ተወልደናል፤
ከማይጠፋው ዘር ተገኝተናል፤
ክርስቶስ ፍቅርን አስተምሮናል።

(//፳፻፮ /)

Friday, May 9, 2014

ልዩ ናት!

ሰይጣን፥ በፈጣሪ መኖር ያምናል፤
ስቶ፥ ለማሳሳትም ቡዙ ይደክማል፤
ከቅዱስ ቃሉም፥ ጥቅስ ይጠቅሳል፤
ቅሉ፥ ይጐለዋል የሃይማኖት ኃይል።

እኔ ሰይጣንን እንዴት ልምሰለው፤
በኤልሻዳይ፥ መኖር የማምነው።

ቅዱሳኑን፥ ለማጥላላት፣ ያለ አግባብ ቃሉን መወርውር፤
ከአምላኬ ነጥዬ፣ እናቱን ላለመቀበል ኅሊናን ማስነውር፤
ላልተገባ ነገር፥ ጥቅስ መጠቃቀስ፣ ብዙ ጊዜ መዳከር፤
ሰይጣን፥ ይለየኛል ከሕይወት ቃሉ፣ ከክርስቶስ ፍቅር።
 
ዲያብሎስ፥ ይጎለዋል፣ የሃይማኖት እምነት፤
ለምን? ልምሰለው፥ ከእርሱ ጋር በሕብረት።

ሰይጣን፥ ቃሉን ያውቃል ኃይሉን ይክዳል፤
እንደተባለው፥ እጅግም ይንቀጠቃጥማል፤
ያኔ ክርስቶስ የዳዊት ልጅ ተብሎ ተነግሯል፤
ዛሬማ፥ ይኼ እጹብ ድንቅ ቃል ይናፍቀናል።

ዓይኑ እንዲያይ የዳዊት ልጅ ብሎ፤
የአባቶቹን ፈለገ-መንገድ ተከትሎ።

ሕያው ቃሉ፥ ማርያም እናቱ እንደኾነች፤
ያስረዳናል፥ በአምላክ እንደተመረጠች፤
ልዩ ናት! ድንግል እናታችን ለምስራች፤
ከመልአኩ ገብርኤል ሥሙን የሰማች።

እናንተ ሰይጣናት ከእኔ ተፋቱኝ፤
ስለ እናቱ ልዕልና መስካሪ ነኝ።

እኔስ የምለየው፥ ከሰይጣን ምስክርና ማህበር፤
የዳዊት ልጅ፣ የድንግል ልጅ ስል ነው በፍቅር፤
ቃሉ ያስገድደኛል፥ ስለ ቅዱሳኑ እንድመሰክር፤
እንዲከብሩ እርሱ ለመረጣቸው እግዚአብሔር።

ከሕይወት ምንጭ፥ በቃሉ ነፍሴ እንዲኖር፤
እመስክራለሁ፥ በሕያው ጥላ ሳልጠራጠር።

እስኪ ንገሩኝ፥ ጥፋቴ ምኑ ላይ ነው?
ምንድን ነው ኃጢያቴ? እኔስ እላለው፤
የድንግል ልጅ ኢየሱስ፥ በሥጋ የተወለደው፤
ክርስቶስ፥ የተዋሕደው በቀረልን ዘር ነው።

<<ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወድንግል ማርያም ክብር፤ አሜን>>
(//፳፻፮ /)

Thursday, April 17, 2014

ታትመናል፥ በደሙ በክርስቶስ!


ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ፥ የዓለም መድኃኒት፣
ተወልዶ፥ ከድንግ ማርያም ቅድስት፣
ፍቅሩን ሲገልፅላት፥ እነሆ፦ እናቴ አላት፣
እኛም እንበላት፥ በክርስቶስ ፍቅር እናታችን ናት።

ክርስትና፥ ኦርቶዶክ ዘ ተዋሕዶ ነች፣
የቅዱሳኑን ስማቸው፥ ታከብራለች፣
ከክርስቶስ ስርዓት፥ ያልበረዘች፣
ሁሉን ነገሯን፥  ስለ እርሱ ያደረገች።

መጥምቁ ዮሐንስ፥ ክርስቶስን ሲሰብከው፣
የዓለም በግ፥ መድኅነ ኢየሱስ ነው ሲለው፣
አይሁድ ፈሪሳዊያን፥ ለካስ ሞኞች ናቸው፣
አፍጥነው ለመስቀል፥ እቅድ አዘጋጅተው።

በተና በ ተመካ ሉ፣
ሁከት እንዳይነሣ በበዓል አይሁን አሉ።

ዕረቡ፥ የከንቱ ከንቱ ምክር ተፀነሰ፣
ቀኑ ጸጥ ብላ ዋለች ዕት ሐሙስ፣
በዚች ሌሊት ተያዘ የዓለም ንጉስ፣
ዓለሙን በደሙ ሊያነፃ ክርስቶስ።


Tuesday, April 8, 2014

የሌሊቱ ተማሪ

ከፍሪሳዊ ወገን፥ የአይሁድ አልቃ የሆነው፤
ከሕገ ልቦና እስከ ሕገ ኦሪት የተማረው

ኒቆዲሞስ የሌሊቱ ተማሪ
ሕጉን ሥርዓቱን አክባሪ
በሙኩራብ ቃሉን መስካሪ
ቅዱሳት መፅሐፍትን መርማሪ

የሌሊቱ ተማሪ፥ ምጡቅ ዕውቅት ቢኖረው
ያላወቀውና ያለተረዳው፥ ጉድለት ነበረው
ስለዚህ፥ የሃይማኖቱን ጉድለቱን ሊሞላው
ለሕሊናው እረፍት መላ ፈለጎ  አገኘው

ያሰላሰለ በሌሊቱ ጨልማ 
ለነፍሱ ጥማት ቃሉን ሊስማ
ይኼድ ነበር ወደ ቃሉ አውድማ
ቀረበ፥ ኢየሱስም ድምፁን አሰማ

ሠው ዳግምኛ ከውኃና ከመንፈስ
ይወለድ አለ የእኛ አምላክ ኢየሱስ

የሠውን ሠውነት የተዋሕደው
ለዓለም ኹሉ መድኃኒት የነው
ለኒቆዲሞስ ምስጢረ ጥምቀት የነገረው
የድንግል ዘር ኢየሱስ ክርስቶስ ነው!

ሠው ዳግምኛ እንዲወለድከውኃና ከመንፈስ
ነገረ ማና ለሌሊቱ ተማሪ ለኒቆዲሞስ

(ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወድንግል ማርያም ክብር!)