Sunday, April 20, 2014

ክርስቶስ፥ በከርሰ መቃብር፤ ሦስት መአልት ሦስት ሌሊት እንዴት ሊሞላው ቻለ? በቀሲስ ብርሃኑ ጎበና

        ክርስቶስ ሦስት መአልት ሦስት ሌሊት፣ በከርሰ መቃብር አደረ፤ የሚባለው፥ እንዴት ሆኖ ነው? (ለሚለው ጥያቄ፥ ምላሹ በሁለት ዓይነት አረዳድ እንገነዘባለን)

        
፩፤ ለዚህ ምላሽ የዕብራውያንን አቆጣጠር ማወቅ ያስፈልጋል:: የመጽሐፍ ቅዱስን ምስጢር ለማወቅ መጽሐፍ ቅዱስን የጻፉት የዕብራውያንን ሥርዓት ወግና ጂኦግራፊያዊ (መልክአ ምድራዊ) አቀማመጥ ያስፈልጋል።

        
ምክያቱም፥ ጸሐፊዎቹ ባህላቸውንና ሥርዓታቸውን ጠብቀው የጻፉት ስለሆነ ነው። ጌታ ዓርብ ተሰቅሎ ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ ከተነሳሣ እንዴት ብሎ ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት ይሞላል ሊያሰኝ ይችላል።

        
ዕብራውያንን አቆጣጠር ሌሊት የሚቆጠርው በዋዜማው ካለው አሥራ አንድ ሰዓት ጀምሮ ነው። ከአሥራ አንዱ ሰዓት በፊት ያሉት ሰዓቶች ግን አንድ ሰዓትም ቢሆን እንደ አንድ መዓልትና ሌሊት ይቆጠራል። ጌታ የተቀበረው ዓርብ ከአሥራ አንድ ሰዓት በፊት ስለሆነ የተቀበረበት ሰዓት የዓርብን መዓልትና ሌሊት ያጠቃልላል።

        
አርብ ከሠርክ አሥራ አንድ ሰዓት ጀምሮ እስከ ቅዳሜ አሥራ አንድ ሰዓት ከሰዓት በዋላ ድረስ ያለው የቅዳሜ መዓልትና ሌሊት ነው። ቅዳሜ ከአሥራ አንድ ሰዓት ጀምሮ ያለው እሑድ ነው። አንዱም ሰዓት ቢሆን ከላይ እንደ ተገለጠው የዕለቱን ሰዓቶችን ያሟላል። ጌታም የተነሣው እሑድ በመንፈቀ ሌሊት ስለሆነ ሦስት መዓልት ሶስት ሌሊት ይሆናል።

        
፪፤ ሁለተኛው ደግሞ የተሰቀልው በዕለተ አርብ ሰለሆነና የሞተውም በዕለት አርብ በመሆኑ አቆጣጠሩ ከአርብ ጠዋት ይጀምራል። አርብ ጠዋት ከ፲፪ ሰዓት እስከ ሰዓት ድረስ በምድር ላይ ብርሃን ነበር፤ አንድ ቀን።

        
ከ፮ እስከ ሰዓት በምድር ላይ ጨለማ ሆነ ይላል መጽሐፍ ቅዱስ፤ ያም፥ ጨለማ እውነተኛ ጨለማ እንጂ በምትሐት የሆነ ስላልሆነ እንደ ሌሊት ይቆጠራል። አንድ ቀን አንድ ሌሊት ይኖረናል። አርብ ከ፱ ሰዓት እስከ ምሽቱ ፲፪ ሰዓት እንደገና ቀን ሆኖአል፤ አርብ ሌሊት ለቅዳሜ አጥቢያ ያለውን ጨለማ ወይም ሌሊት ስንቆጥር ሁለት ቀን ሁለት ሌሊት ይሆናል።

        
ቅዳሜ ሙሉ ቀንና ሌሊት ለእሁድ አጥቢያ ጌታ እሁድ ሌሊት ተነስቷል፤ አንድ ላይ ሲደመር ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት ይሆናል። እንግዲህ በሁለቱም ዓይነት የሚቆጥሩ ስላሉ ሁለቱም ዓይነቶች ቀርበዋል እኛም የገባንና የተረዳንን አቆጣጠር መርጠን ማስረዳትም መረዳትም እንችላለን።

                     
<<<<<<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! >>>>>>>>

ምንጭ፦ ዓምደ ሃይማኖት /ገፅ ፹፱/ ሲስ ብርሃኑ በና

Thursday, April 17, 2014

ታትመናል፥ በደሙ በክርስቶስ!


ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ፥ የዓለም መድኃኒት፣
ተወልዶ፥ ከድንግ ማርያም ቅድስት፣
ፍቅሩን ሲገልፅላት፥ እነሆ፦ እናቴ አላት፣
እኛም እንበላት፥ በክርስቶስ ፍቅር እናታችን ናት።

ክርስትና፥ ኦርቶዶክ ዘ ተዋሕዶ ነች፣
የቅዱሳኑን ስማቸው፥ ታከብራለች፣
ከክርስቶስ ስርዓት፥ ያልበረዘች፣
ሁሉን ነገሯን፥  ስለ እርሱ ያደረገች።

መጥምቁ ዮሐንስ፥ ክርስቶስን ሲሰብከው፣
የዓለም በግ፥ መድኅነ ኢየሱስ ነው ሲለው፣
አይሁድ ፈሪሳዊያን፥ ለካስ ሞኞች ናቸው፣
አፍጥነው ለመስቀል፥ እቅድ አዘጋጅተው።

በተና በ ተመካ ሉ፣
ሁከት እንዳይነሣ በበዓል አይሁን አሉ።

ዕረቡ፥ የከንቱ ከንቱ ምክር ተፀነሰ፣
ቀኑ ጸጥ ብላ ዋለች ዕት ሐሙስ፣
በዚች ሌሊት ተያዘ የዓለም ንጉስ፣
ዓለሙን በደሙ ሊያነፃ ክርስቶስ።


Tuesday, April 8, 2014

የሌሊቱ ተማሪ

ከፍሪሳዊ ወገን፥ የአይሁድ አልቃ የሆነው፤
ከሕገ ልቦና እስከ ሕገ ኦሪት የተማረው

ኒቆዲሞስ የሌሊቱ ተማሪ
ሕጉን ሥርዓቱን አክባሪ
በሙኩራብ ቃሉን መስካሪ
ቅዱሳት መፅሐፍትን መርማሪ

የሌሊቱ ተማሪ፥ ምጡቅ ዕውቅት ቢኖረው
ያላወቀውና ያለተረዳው፥ ጉድለት ነበረው
ስለዚህ፥ የሃይማኖቱን ጉድለቱን ሊሞላው
ለሕሊናው እረፍት መላ ፈለጎ  አገኘው

ያሰላሰለ በሌሊቱ ጨልማ 
ለነፍሱ ጥማት ቃሉን ሊስማ
ይኼድ ነበር ወደ ቃሉ አውድማ
ቀረበ፥ ኢየሱስም ድምፁን አሰማ

ሠው ዳግምኛ ከውኃና ከመንፈስ
ይወለድ አለ የእኛ አምላክ ኢየሱስ

የሠውን ሠውነት የተዋሕደው
ለዓለም ኹሉ መድኃኒት የነው
ለኒቆዲሞስ ምስጢረ ጥምቀት የነገረው
የድንግል ዘር ኢየሱስ ክርስቶስ ነው!

ሠው ዳግምኛ እንዲወለድከውኃና ከመንፈስ
ነገረ ማና ለሌሊቱ ተማሪ ለኒቆዲሞስ

(ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወድንግል ማርያም ክብር!) 

Friday, March 21, 2014

ተግሣጽን አትቀበሉምን? /ኤር 35፥13/



የክብሩ ሞገሥ፦ በሠማያት፣ በምድር፣ በጥልቁም ሥፍራ ያለ፤ እግዚአብሔር ለፈጠረን ፍጥረቱ (በተለይ ለእኛ በአምሳሉ ለፈጠረን ሠዎች) ስለሚወደንና ስለሚያፈቅረን ይገሥጸና! በነጐድጓድና መባርቅት፣ በከባድም ደመና ድምፅ፣ በብርቱ የንፋሳት ውሽንፍር ድምፅ፤ እግዚአብሔር፥ ህዝቡን ይገስጻል!።

ከነዚህ፥ ከተፈጥሮ ተግሣጽ ይልቅ ግን ተግሣጽን በአንደበተ-ቃል (ከሠዎች በሚወጣ ቃል) ሲገሥጽ በብሉይም በሐዲስም እናያለን። ለምሳሌ ያህል፥ በብሉይ፦ እግዚአብሔር፥ በሚወዳቸውና እንደ ሐሳቡና እንደ ትህዛዛቱ የሚሄዱትን አገልጋዮቹን በመላክ፣ በነቢዩ ኤርምያስ አንደበት አድሮ፦ ተግሣጽን አትቀበሉምን? /ኤር 35፥13/ እያለ ያናግር ነበር እናነባለን።

ይህ ተግሣጽ፥ በብሉይ ብቻ ሳይሆን በሐዲስ ኪዳንም ቢሆን የምናገኘው እውነታ ነው! ይህ የተግሣጽ እውነታ ደግሞ እራሱ ባለቤቱ፦ የፍቅር አምላክ፣ የተግሣጽ ጌታ፣ መድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስም በመዓክለ ምድር ከእናታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በስጋ ተወለዶ፣ (ከበረት ውስጥ መወለድ ጀምሮ እስከ በዓለ ዕርገት፤ የተተረከውን ብናነብና ብናስተውል፣ በመንፈሳዊ ዕይታ ብናያቸው፣ ፍቅርን ብቻ ሳይሆን ተግሣጽ እናገኛለን! ) ሲያስተምርና ይህንን ዓለም በፍቅሩ አቅርቦ፣ በተግሣጹ ገሥጾ፤ ሕይወትን እንድናገኝ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያት እንዲህ ሲል ጥያቄ አቀረበላቸው፦ "ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል?" ብሎ ሲጠይቅ፥ ሐዋርያትም በፈሪሳውያንና በሰዱቃውያን፣ እንዲሁም በአይሁድ ረበናት ካህናት የሚባለውንና የሚናገሩት ቀድመው ስለሰሙ፦ "አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው፤ ይላሉ አሉት።"

Thursday, March 20, 2014

በመልአከ መንክራት ግርማ ወንዱሙ ላይ ማጉረምረም ለምን?


አንዳንድ ወንድሞችና እኅቶች በመልአከ መንክራት ግርማ ወንዱሙ ትምህርት ቢመሰጡም፤ የተስጧቸው፥ ያህል ግን አጥጋቢ መንፈሳዊ ስንቅ ያለመያዛቸው ጉዳይ በተጠይቅና በፍልስፍና ጥያቄዎች ሲዳክሩ ማየት የተለመደ ነው።

እንዚህ ሠዎች የዲያቢሎስ መንፈስ ስልትና ውጊያ አለማገናዘባቸው፣ በመንፈሳዊ ትምህርታቸው ውስጥ የሚያስተላልፉት መንፈሳዊ ትምህርቶች ወደጐን በመተው፤ ከአምላክ የተቸራቸውን የጸጋ ሃብተ-ፈውስን በመንተራስና በመለጠጥ፣ አጉልተው፥ ለማጣመምና ሃብተ-ፈውስን "በአጋንት አለቃ አጋንትን የሚያወጣ ሠው ናቸው" በማሰኘት፣ ከመንፈሳዊ ዕይታ ይልቅ በኢ-መንፈሳዊ ዕይታዎች በማቀናጀት፣ ለማጣጣልና ከእግዚአብሔር ጸጋ-በረከት ህዝቡ እንዲርቁ በአሳቻ ምክር በመምከርና በክፉ ዕይታ እንዲታዩ በማሳየት፤ ትልቁን፥ የማጥመቅ አገልግሎት ማለትም፦ ከቤተ-ክርስቲያን ምስጢራት አንዱ "ምስጢረ ጥምቀት" የወጣ ነው፤ ብለው፥ ሲያወሩና ሲፅፉ እያየን ነው።

ቢሆንም ምስጢረ ጥምቀት ከቤተ-ክርስቲያን ምስጢራት አንዱና ዋነኛው ሲሆን፤ እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ ሆነና ስለ ምስጢረ ጥምቀትን (-አማናዊ የሆኑ ሠዎች፦ ወደ ክርስትና ሊመጡ ቢወዱ ንስሐንና ክርስትና እንዲነሱ ሲፈቅዱ የሚያደርጉትን የቀኖና ስርዓት ከምስለ ወድምፅ VCD 1-27 እንዲሁም መፅሐፋቸው፣ በተጨማሪም በአቢሲኒያ የሚተላለፈው በመንፈሳዊ ትምህርታቸው የተካተተ ነው!) በተለይም እንዴት እንደሚፈጸም በ፪፯ኛው በምስለ ወድምፅ በየረር ቅድስት ሥላሴ ቤተ-ክርስቲያን በአውደ ምዕረት ላይ በተካሄደው ንስሐ ክርስትና እንዴት በቤተ-ክርስቲያን ምስጢራት እንደሚከናወን፤ የተገለጸና የታመነ በቂ ምስክር ነው!

እግዚአብሔር፥ ጸጋ በረከታቸውን ያብዛልን፤ እርሳቸውንም ከሠዎች ከንቱ ውዳሴና ከንቱ ማጉረምረም በተጋድሎና በጽናት ያቆይልን፤ አሜን!

Sunday, March 2, 2014

ግብረ-ሰዶማውያንና የባህድ ስውር መነፅር፤ ለሃገራችን አይበጃትም!



ሚኒስትር / ዘነቡ ሆኑ የኢአህዴግ ባለስልጣናት እንዲሁም የፖለቲካ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ቢሆኑም በግብረ-ሰዶማውያን ላይ በአፅኖት ማስገንዘብ አለባቸው። ዳር-ዳር ማለት አያዋጣም!

እውነት ነው ኢትዮጵያ የሴቶች፣ የወጣቶች፣ የሕጻናትና የእናቶችን ነገር በተመለከተ፤ ቡዙ የብዙ፣ ሕጎቿን በማጥበቅ እና እጅግ አድርጋ አርቅቃ መስራት ይጠበቅባታል እንጂ ለአስጸያፊ ድርጊት የአሜሪካንንና የአውሮፓ ሃገራትን የሞት ምኞት ማስተናገድም ይሁን በር መክፈት የለባትም!

እርግጥ ነው፤ በመንግስ መገናኛ-ብዙሃን፦ ስለ ግብረ-ሰዶማውያን አስከፊነት፣ የነውር ድርጊት መሆኑን፣ የሥነ-ልቦና ቀውስ እንደሚያስከትል፣ በዚህ አስጸያፊ ድርጊት የገቡና የኖሩ ሰዎች ለተለያየ በሽታዎች የመያዛቸው ዕድል በጣም ከፍ-ያለ ሰፊ መሆኑን፣ በጭንቀትና በውጥረት መሰቃየታቸው እንደሚጨምር፣ እራስ-በራስ የማጥፋት ደረጃ በነዚህ ሰዎች ላይ ቁጥሩ እንደሚያይል፣ አጠቃላይ ግብረ-ሰዶማውያን አስከፊነትና መራራነት፤ በዜና አውታራቸው አለመዘገባቸው፤ ወዴት እየሄድን ነውም? ያሰኛል!

ወዳጆች ሆይ፦ በውጭ ዓለማት ላላቹ፤ በተለይ ደግሞ በአሜሪካና በአውሮፓ ሃገራትን ያላቹ! ዘመኑ ከባርነት ዘመን ወደ ዲሞክራሲያዊ ባርነት ዘመን (ከሃገራችን የወጣንበት የተለያየ ምክንያት ቢኖረንም) ላይ መድረሳች ይታወቃል። ይህን ስል፥ ማንም ቢሆን ሃገሩ ላይ መኖን የሚጠላ ሠው ያለ̕ አይመስለኝም።