Monday, June 17, 2013

አስሩ ምርጥ ብሒላዊ ምክር፦

1 ሐሜት፦ ያለ መሣሪያ ሰውን መግደል ነው።

2 ማጉረምረም፦ ባገኙት በቃኝ ብሎ አለማመስገን ነው።

3 ቁጣ፦ ከስድበ የሚያደርስ የክፉ አድራጎት መሠረት ነው።

4 ብስጭት፦ የተበሳጩበትን ነገር ሳይሆን ተመልሶ ራስን የሚጎዳ መርዝ፣ ከክህደት የሚያደርስ የኃጢያት     ምንጭ፤ ጭንቀትን የሚያነድ ትንሽ ክብሪት ነው።

5 መዋሸት፦ እውነተኛ ሠው ሳይታዩ የሚጎዱበት ረቂቅ የሰይጣን ጦር ነው።

6 መርገም፦ አቅም ሲያን ወደ ላይ የሚወረወር የደካማ ሰዎች ቀስት ነው።

7 መሳደብ፦ ህሊናን የሚያቆስል ቁስሉ ቶሎ የማይድን አቅም የሌላቸው ሰዎች ዱላ ነው።

8 ዋዛ ፈዛዛ፦ በስልት የሚቃኙት የሥራ ፈቶች ገበና ነው።

9 የማይገባ ሳቅ፦ ሐላፊ አገዳሚውን የሚያጠመዱበት የአመንዝራዎች ወጥመድ ነው።

10 መሳለቅ ፦ በአካል ጉዳተኛ ሰው ላይ የሚዘበቱበት የመርገም ስንቁ ወግ ነው።

ዋቢ መፅሐፍ ፦ ያለ ጭንቀት የመኖር ምስጢር

No comments:

Post a Comment