Tuesday, June 18, 2013

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መድኃኒታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው የሚናገረውን?


        ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በተለያየ መልክቶቹ "ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።" /ገላ 614/ ቢል "ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ የተረገመ ይሁን።" /ገላ 18/ ቢለን እንኳን በአንድም በሌላም መንገድ ስለቅዱሳን ይሁንም ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሳይነግረን፣ ሳያስተምረን፣ ሳይሰብከን፤ ግን አላለፈም።

        ለዚህ ደግሞ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንጦስ ክርስቲያኖች ባስረዳቸው እውነተኛ አስተምህሮ ድንግል ማርያም ንጽሕት፣ ድንግል መሆኗን፤ መስክሯል። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ለክርስቶስ አገልግሎት በተጠራበት ግዜ "እንደ ንጽሕት ድንግል እናንተን ለክርስቶስ ላቀርብ ለአንድ ወንድ አጭቻችኋለሁና" /2ኛ ቆሮ 11 2/ ይላል። ታዲያ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በትንቢተ ሕዝቅኤል /44 2/ የተነገረውን የእግዚአብሔር ቃል ደግሞ ሲናገር እመቤታችን ድንግል ማርያም ንጽሕት፣ ድንግል፣ ለክርስቶስ በክርስቶስ እንደሆነች አስረግጦ አስረድቶናል።

"ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ አንተ ታውቃለህ" ሕዝ 37፥3 M/ Paulos MelekaSelase


        እግዚአብሔር ሁሉን ያውቃል! ስንወድቅ ስንነሳ፥ እግዚአብሔር ያውቃል!!! መግባት መውጣታችን ያውቃል። ማግኘት ማጣታችን ያውቃል። መውደቅ መነሳታችን ያውቃል። መብላት መጠጣታችንን ያውቃል። መራብ መጥገባችን ያውቃል። መጠጣት መርካታችን ያውቃል። ጥማታችንን ያውቃል። እግዚአብሔር ሁሉን ያውቃል!!!

        አቤቱ፥ አንተ መቀመጤንና መነሣቴን አንተ ታውቃለህ፤ መንገዶቼን ሁሉ እነሆ የቀደመውንና የኋላውን ሁሉ አንተ ታውቃለህ!!! (መዝ 138/9 1-6) / ጳውሎስ መልክዓ ሥላሴ (B. Th)

         "ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ አንተ ታውቃለህ" ሕዝ 373  በሚል (ሰባኪ ወንጌል ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ) በመ/ ጳውሎስ መልክዓ ሥላሴ (B. Th) የተሰጠ መንፈሳዊ ትምህርተ ወንጌል ተመልክተው ስጋዎትንና ነፍሶትን ይመግቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ስም ተጋብዘዋል።


Monday, June 17, 2013

አስሩ ምርጥ ብሒላዊ ምክር፦

1 ሐሜት፦ ያለ መሣሪያ ሰውን መግደል ነው።

2 ማጉረምረም፦ ባገኙት በቃኝ ብሎ አለማመስገን ነው።

3 ቁጣ፦ ከስድበ የሚያደርስ የክፉ አድራጎት መሠረት ነው።

4 ብስጭት፦ የተበሳጩበትን ነገር ሳይሆን ተመልሶ ራስን የሚጎዳ መርዝ፣ ከክህደት የሚያደርስ የኃጢያት     ምንጭ፤ ጭንቀትን የሚያነድ ትንሽ ክብሪት ነው።

5 መዋሸት፦ እውነተኛ ሠው ሳይታዩ የሚጎዱበት ረቂቅ የሰይጣን ጦር ነው።

6 መርገም፦ አቅም ሲያን ወደ ላይ የሚወረወር የደካማ ሰዎች ቀስት ነው።

7 መሳደብ፦ ህሊናን የሚያቆስል ቁስሉ ቶሎ የማይድን አቅም የሌላቸው ሰዎች ዱላ ነው።

8 ዋዛ ፈዛዛ፦ በስልት የሚቃኙት የሥራ ፈቶች ገበና ነው።

9 የማይገባ ሳቅ፦ ሐላፊ አገዳሚውን የሚያጠመዱበት የአመንዝራዎች ወጥመድ ነው።

10 መሳለቅ ፦ በአካል ጉዳተኛ ሰው ላይ የሚዘበቱበት የመርገም ስንቁ ወግ ነው።

ዋቢ መፅሐፍ ፦ ያለ ጭንቀት የመኖር ምስጢር

Saturday, June 15, 2013

በመጽሐፍ ቅዱስ እይታ "ባርያ" ማለት ምን ማለት ነው?


ወዳጆች ሆይ ቅድስት ድንግል ማርያም ልጅ  በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሠላምና ፍቅር ይሁንላቹ!

* በመጽሐፍ ቅዱስ ያ ማለት በብዙ መንገድ የየራሱ ታሪክና ጥልቅ የሆነ ሐተታን ቢጠይቅም እኔ ግን እግዚአብሔር እንደ ፍቃድ በሦስት አበይት የሥአገልግ እይታ እንመለከተው ዘንድ እነሆ፦

1ኛ፦ በፊት በነበረው እርዮተ ዓለም ለምድ የሥአገልግዎቹን በቅጥር መልክ ሳይሆን በአስገባሪዎች አማካኝነት የባርነትን ስራ እንደ ህጋዊነት ይሸጡ ይለውጡ እንደነበር  መጽሐፍ ቅዱስ እንዲ ብሎ ይገልጽልናል “በብር የተገዛ ባያ” /ዘ 1244/ እንዲል!  

2ኛ፦ በባርነት ሳይፈልጉና ሳይፈቅዱ በግዳጅ ያለምንም ክፍያ እንዲያውም እየተደበደቡ፣ ስቃይና መከራ እየተቀበሉ፣ እየተገደሉ፣በሚወልዷቸውም ልጆች ጭምር ዓይናቸ እያየ፣ በመሪር ልቅሶና እሪታ አንጀታቸው እየተላወሰ ወንድ ልጆቻቸው ለሞት፥ ሴት ልጆቻቸውን ደግሞ፤ በጽኑ ሥራ፥ በጭቃ፥ በጡብም በእርሻም ሥራ ሁሉ፥ በመከራም በሚያሠሩአቸው ሥራ ሁሉ፥ ሕይወታቸውን ያስመርሩአቸው እንደነበር፥ እንዲሁም ግብፃውያን የእስራኤልን ልጆች በመከራ እንደገዙአቸው። መጽሐፍ ቅዱስ በሰፊው ያትትልናል። /ዘጸ 1፥ 13-14/

3ኛ፦ ሦስተኛው ደግሞ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የእግዚአብሔር መልአክቶች፣ለሟቹ፣ አገልጋዮቹ፣ ነቢያቶች፣ አጠቃላ ለመንፈሳ አገልግ ሲሉ ራሳቸውን በተጋጋ ይጠሉ። መሆ እንደ እግዚአብሔር ቃል ለመንፈሳዊ አገልግሎት ይህን ቃል የተጠቀሙትን በአጭሩ እንይ፦

Saturday, May 25, 2013

የዶ/ር እጓለ ገብረ ዩሐንስ አጭር የሕይወት ታሪክ

ደራሲ / እጓለ ገብረ ዩሐንስ ከጻፉት መፅሐፍ ስለ ሞራል ድቀት ብፁዓን ንጹሐነ ልበ ስለ ክርስቲያን ምግባር መሠረት በሚል ለንባብ ካበቁት የተወሰደ። 

      ሀገር፣ መንደር፣ ቤት ንብረቱን ትቶ ወደ ሩቅ የሄደ ሰው ባይተዋር ይባላል። ይህ ስያሜ በኑሮ አድራሻ መለወጥ ብቻ ምክንያቱን የሚያገኝ አይደለም።   የመንፈስ ባይተዋርነትም አለ። ሰው ከነበረበት ቦታ ወደ ሌላ ሳይዘዋወርም ለአዲስ አስተሳሰብ፣ ፈሊጥና የኑሮ መልክ ሊጋለጥ ይችላል። አንደኛው እስኪያይል ወይም ሁለቱም እስኪዋሐዱ ድረስ የወትሮው እና የአሁኑ በሕሊና ውስጥ የባላንጣዎች ተቃርኖ ይፈትራሉ።

       እንዲህ ያለ ሰውነት ሲታገል ይቆይና ሲሰለቸው፦ የቸልተኘነት፣ የግዴለሽነት ኢንዲፈረንቲዝም መንፈስ ይሰፍንበታል። ይህ በተለይ የሚገለጸው በሥነ ምግባር መስክ ነው። ሥለታም የነበረው ሥነ ምግባራዊ በሕሊናው ይሰንፋል። የሚመቹ፣ የማይቆረቁሩ፣ የማይጋጩ እንደ ዘዴኝነት፣ ጮሌነት፣ ብልሃተኝነት፤ ያሉ የማይጨበጡ የቀልጣፋ ሰውነት ጠባዮች ያይላል።አስመሳይ፣ አድር ባይ፣ እንደ እምነቱ የማያምን፣ እንደ ኑሮው የማይኖር፣ የሕሊናውን ብኵርና ለምስር ንፍሮ የለወጠሌላም ሌላም። እንደ አለንጋ የሚጋረፉ ተግሣጾች ወቅታዊነታቸውን የሚያገኙት በዚህ ሳቢያ ይመስለናል።የሞራል ድቀትየሚባለው ይህ ሳይሆን ይቀራል? የመነሳቱ፣ የመቆሙ፣ ከራሱ ጋር ተስማምቶ ሚዛን ጠበቆ የመራከመዱ፤ ነገርስ እንዴት ይሆን? ቅን ሕሊና የማያልፈው ጥያቄ ነው።
                           +++++++++++++++++              +++++++++++++++++

Tuesday, April 30, 2013

"ሰሙነ ሕማማት" በዲያቆን ኅብረት የሺጥላ


         ‹‹ሰሙነ ሕማማት›› መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥርዓት ነው፡፡ በርካታ ሰዎች ቤተ ክርስቲያንን ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ የምትጓዝ አካል አድርገው ሊገልጧት ይሞክራሉ፡፡ ይህ እጅግ አላዋቂ መሆናቸውን ይመሰክራል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ከመጽሐፍ ቅዱስ ያልተገኘና በሥጋዊና በደማዊ ዕውቀት ላይ የተመሠረተ ሥርዓት የላትም፡፡ ቅዱስ ሉቃስ በሐዋርያት ሥራ ‹‹ከሕማማቱ በኋላ›› በማለት ስለ ሰሙነ ሕማማት የሚያወሳ ቃል ተጠቅሟል፡፡ (የሐዋ1.3)

            ሰሙነ ሕማማት የሁለት ቃላት ጥምር ውጤት ነው፡፡ ‹‹ሰሙን›› የሚለው ቃል ‹‹ሰመነ›› ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ስምንት ቀኖች ወይም ሳምንት ማለት ው፡፡ ‹‹ሕማማት›› የሚለው ቃልም እንደዚሁ ‹‹ሐመመ›› ወይም ‹‹ሐመ›› ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን መከራዎች ማለት ነው፡፡ ‹‹ሕማማት›› የምንለው ለብዙ ሲሆን ነው፡፡ ለአንድ ወይም ለነጠላ ሲሆን ደግሞ ‹‹ሕማም›› እንላለን፡፡ እንግዲህ ሁለቱን ቃላት በማናበብ ‹‹ሰሙነ ሕማማት›› ስንል ‹‹የመከራዎች ሳምንት›› ማለታችን ነው፡፡

Thursday, April 25, 2013

“ምስጢራዊው ቡድን”

 በመምህር ምሕረትተአብ አሰፋ (የደብረ መዊዕ ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ስብከተ ወንጌል ሐላፊ)

“በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁዋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ፥ ነገር ግን በየዋህነትና በፍርሃት ይሁን።” 1ኛ ጴጥ 3፥15
 

     በዚህ “ምስጢራዊው ቡድን” በተሰኘው ቪሲዲ ትምህርታችን የምንመለከተው በተዋህዶ ጓዳ በክርስትና ዓለም ምሽጋቸውን መሽገው በዲቁናና በቅስና እንዲሁም በምንኩስና ከተቻላቸውም በጵጵስና መሐረግ በየአብያተ ክርስቲያናቱና በየገዳማቱ ተደብቅው ከቆዩ በኃላ ውስጣችን አጥንተው ምስጢራችንን አየተው የስለላ ስራቸውን በማጠናከር ቀን ጠብቅው ጊዜ አመቻችተው እኛ ኮብልለናል እናንተም ኮብልሉ በማለት እንጀራችንን በልተው ተረከዛቸውን በኛ ላይ ስለሚያነሱብን ወገኖች ነው።

        ሃያ ሰባት ዓመት በክርስትናው ዓለም ቆይቻለሁ፥ ክርስትናንም ከእግር እስከ ራሱ መርምርያለሁ ነገር ግን የሚያሳምነኝ ነገር ለህሊናዬ አላገኘሁም በማለት፦ “ጉዞ ወደ ኢስላም” በሚል የኮበለለውን በእንጦንስና በመቃርስ ቆብ የቆመረውን የትላንቱን አባ ወ/ሥላሴ የዛሬው ኻሊድ ካሳሁንን ምስጢራዊ ተልዕኮ መርምረን ላነሳቸው ጥቄዎች መልስ የምንሰጥ ሲሆን በቀጣይነት ልክ እንደ ኻሊድ ካሳሁን “ብርሀናዊው ጎዳና” በማለት የክርስትናውን ዓለምና ክርስትናን በማጠልሸት ለኮበለለው ዳኢ ኻሊድ ክብሮም መልስ የምንሰጥ ይሆናል።

               ከሁሉ አስቀድመን ማስተዋል ያለብን ነገር ቢኖር ሠው የፈለገውንና የመረጠውን እንዲሁም ያመነበትን ማምለክ እንደሚችል ሕገ እግዚአብሔርም ሆነ ሕገ መንግስት በሚገባ ደንግገውታል። ነገር ግን ሠው ከራሱ አልፎ ሌላው ያዋጣኛል ብሎ ያመነበትን ማንቋሸሽና ማጠልሸት ተገቢ ነው ብለን አናምንም።